የበርሃሌ ሰደተኞች መጠለያ ጣብያ ፅ/ቤት ባለ ስድስት ክፍል የሰራተኞች መኖሪያ ቤት በጉልበት ስራ ጨረታ በሚቀርበው ዲዛይን መሰረት ኣወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል ፡፡በመሆኑም

በርሃሌ ስደተኞች መጠሊያ ጣቢያ ፅ/ቤት

1 ህጋዊና የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፤                

2 የወቅቱና የስራ ግብር የከፈሉና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፤

3 በግንባታ ስራ ደረጃ 8 እና ከዚያ በላይ ማንኛውም የግንባታ ስራ ተቃራጭ፤

4 ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ለእያንዳንዱ ግንባታ 2 በመቶ በሲፒኦ ማስያዝ የሚችል፤

5 ጨረታውን ማሸነፉ እንደተገለፀለት ወዲያውኑ ያሸፈነበት ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ ለመልካም ኣፈፃፀም ዋስትና ማረጋገጫ ማቅረብ ለሚችሉ ተወዳዳሪዎች በሙሉ፤

6 ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ07 ተከታታይ የስራ ቀናት እስከ 19/09/2011ዓ/ም ከጧቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ክፍት ሆኖ ተጫራቾች በበራህሌ ስደተኞች መጠሊያ ጣብያ የመሰብሰቢያ ኣደራሽ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እየገለፀን በቀን 19/09/2011ዓ/ም ከጧቱ በ4፡00 ታሽጎ ከጧቱ በ04፡30 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በበራህሌ ስደተኞች መጠሊያ ጣቢያ የመሰብሰቢያ ኣዳራሽ ውስጥ በግልፅ ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ተጫራቾች በፖስታው ላይ በሌለሁበት ይከፈት ብለው ከገለፁ ኮሚቴው ፖስታውን የሚከፈት መሆኑን እንገልፃለን፡፡

1 ተጫራቾች ለኣንድ የግንባታ ኣይነት በማይመለስ 100.00 ብር ሰነድ በመግዛት መወዳደር ይችላሉ፤

2 ከላይ ለተገለፀው የግንባታ ኣይነት ለእያንዳንዱ ብሎክ በመለያየት በሰነድ ኣስደግፈው በተለያየ ፖስታ ሙሉ ስምና ኣድራሻና በግልፅ ፅፈው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

3 ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት የግንባታ ኣይነት ኦርጂናል ዶክመንት ከኣንደ ኮፒ ጋር ማሰገባት ይኖርባቸዋል፡፡

4 ተጫራቾች ለሚያቀርቡት የግንባታ ኣይነት ኦርጂናል ዶክመንት ከኣንደ ኮፒ ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

5 መ/ቤቱ የተሻለ ነገር ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስ.ቁጥር 0914-709899/0910-562429 ደውለው መጠየቅ ይቻላል፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo