በአገር መከላከያ ሚኒስቲር የሰሜን ዕዝ ሎጅስቲክስ ሜን/ኢን/ሪክ/መምሪያ ግዥ ክፍል በ2011 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተገለፁትን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

መከላለያ ሰሜን ዕዝ ጠ/መምርያ

ቁጥር ሰ/ሰ/ሜን/ኢን/ሪከ/መም/ 

ግዥ 02/2011 

በአገር መከላከያ ሚኒስቲር የሰሜን ዕዝ ሎጅስቲክስ ሜን/ኢን/ሪክ/መምሪያ ግዥ ክፍል በ2011 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተገለፁትን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ 

  1. ሎት 1 የተለያዩ የኮንስትራክሽን ዕቃዎች 
  2. ሎት 2 የተለያዩ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች 
  3. ሎት 3 የተለያዩ የቧንቧና ሳኒተሪ ዕቃዎች 
  4. ሎት 4 ጠጠርና አሸዋ 

በዚህም መሠረት በዘርፉ የተሰማሩ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት የቫት ሰርተፍኬት እና የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፍኬት ያላቸውን ይጋብዛል፣፣ ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መመሪያና ዝርዝር ሰነድ የያዘ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 4 ለእያንዳንዳቸው ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት መቐለ ወደ አዲግራት በሚወስደው መንገድ መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ መታጠፊያ ሰሜን እዝ ሎጅስቲክስ መምሪያ ግዥ ክፍል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመግዛት በቢሮው ወደ ተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ጨረታው ግንቦት 17 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

ለተጨማሪ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር፡-034-2400002/0920426802 

በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን 

ዕዝ ጠቅ /መምሪያ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo