ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ/የተ/የግ ማህበር በመቐለ ዋና መ/ቤት ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ሞዴል ፎቶ ኮፒዎች፣ ፕሪንተሮች፣ ፋክስ ማሽኖች እና ኮምፒተሮች ሲበላሹ የጥገና ኣገልግሎት ለማግኘት በጨረታ ኣወዳድሮ ውል ለማሰር ይፈልጋል፡፡

ትራንስ ኢትዮጽያ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

1 ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ የ2011ዓ/ም ያላቸውና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆን ኣለባቸው፣/ የማስረጃው ፎቶ ኮፒ ማያያዝ ያስፈልጋል/

2 ተጫራቾች በዚሁ ስራ የተሰማሩ መሆናቸውን ማረጋገጫ ማቅረብ ኣለባቸው፤

3 ተጫራቾች የጨረታ ዋጋ ሲያስገቡ በጨረታ ስነዱ በተገለፀው ስፔስፊኬሽን መሆን አለበት፣ እንዲሁም ክፍያ ሲፈፀምላቸው ሕጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

4 የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 50 /አምሳ ብር/ በመክፈል ከመቀሌ ዋና መ/ቤት ከግዢ፣ ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮ በስራ ስዓት መውሰድ ይችላሉ፣

5 የጨረታ ማስከበሪያ ከጠቅላላ ያስገቡት ዋጋ 2% በትራንስ ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ ማህበር ሰም በሲፕኦ (CPO) መልክ ማስያዝ ይኖርባቸዋል:

6 ኣሸናፊ ተጫራቾች ማሽኖቹ የሚጠግኑበት ቦታ መቐሌ ዋና መ/ቤት ቅጥር ግቢ ሲሆን፣ ለሚሰሩት ጥገናዎች ክፍያ የሚፈፀምላቸውም እቃዎች ኢንስፔክት ተደርገው የገቢ ደረሰኝ ከተቆረጠላቸው በኃላ መሆኑ ተጫራቾች ኣስቀድመው ማወቅ ኣለባቸው፡፡

7 ተጫራቾች በተሰጣቸው ሰነድ ውስጥ ብቻ ዋጋቸውን ሞልተው በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ እስከ ግንቦት 13 ቀን 2011 ዓ.ም ከጥዋቱ 4፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ መቀሌ በሚገኘው የግዢ፣ ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው::

8 ጨረታው በዚሁ ቀን ማለትም ግንቦት 13 ቀን 2011 ዓ.ም ዓ.ም ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመቀሌ ዋና መ/ቤት በተመሳሳይ ስዓት ይከፈታል:: በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ የተሟላ ከሆነ ጨረታው በተጠቀሰው ሰዓት ይከፈታል::

9 ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

10 ተጨማሪ ማብራርያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 034-441 64 39 / 034-440 82 05 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ::

ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ ማህበር

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo