የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የስደተኞች ተፅእኖ ምላሽ ልማት ፕሮጀክት (DRDIP) ከዚህ በታች የተጠቀሱት የኤሌክትሮኒክስና ተዛማጅ ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ (NCB) አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ

ሎት 1፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች

1 በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ደኩሜንት ለያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ከ16/8/2011 ዓ.ም ጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮኣችን የግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፤ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል።

2 የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የVat ሰርቲፊኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (Tin) እና ያለፈው ወር ቫት (Vat) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት።

3 ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው።

4 የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) በጨረታ)ደኩሜንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ (CPO) አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

5 ቢሮኣችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 15% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው። ጨረታው 15/9/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮኣችን የዕቃ ግዥ ክፍል ይከፈታል።

6 ቢሮኣችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

7 ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልክ ቁጥሮች 034 440 36 63/ 034 440 43 46 ወይም በፋክስ ቁጥር 034 440 99 71/034 440 36 63 መጠየቅ ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo