ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም አ/ማ ለ2011 ዓ/ም የድርጅቱ ሒሳብ በጨረታ አወዳድሮ ኦዲት ለማስደረግ ይፈልጋል፡፡ ስለዚ ለመጫረት ለምትፍልጉ የኦዲት ድርጅቶች /Audit Firms/ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርት የምታሟሉ እንድትወዳደሩ እንጋብዛለን፡፡

ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም

1 ተጫራቾች የጨረታው ፍቃድና የ2011ዓ/ም የመ/ት ግብር የስራ ማስረጃና ቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን ማቅረብ የሚችሉ፤

2 ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ የሚሆን ከጠቅላላ 2 %በባንክ የተረጋገጠ ሲፒሶ ብቻ ማስያዝ ይኖርባችዋል:: ከ2 % በታች ያስያዘ ከጨረታ ውጭ ይሆናል፡፡

3 ተጫራቶች የጨረታ ዶክሜንት መቐለ በሚገኘው ዋና መስሪያቤታችን ደደቢት ብድርና ቁጠባ አ/ማ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 409 ወይም ኣዲስ ኣበባ በሚገኘው ተ/ሃይማኖት ቅርንጫፋችን 100.00 /መቶ ብር/ በመክፈል ከ 16/08/2011 ዓ/ም ጀምሮ  የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ::

4 ለመጫረት የምትፈልጉ ተወዳዳሪዎች የምትሰሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ መቐለ ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን እስከ ግንቦት 02/2011ዓ/ም ከቀኑ 3፡00 ሰዓት ማስገባት ትችላላችሁ፡፡

5 የድርጅቱ ሒሳብ ስራ በትግርኛ እና በኢንግሊዝኛ ቋንቋ ስለሆነ ተጫራቾች ይህንን ግምት ውስጥ በማስገባት ሊሰሩ የሚችሉ መሆኑን ማወቅ ይኖርበታል፡፡

6 ጨረታው 02/09/2011 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡00 ተዘግቶ በድርጅቱ የቀረበውን ሰነድ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት እንዲሁም የተሟላ ዶኩሜንቱ ከሆነ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በይኖሩም ከጥዋቱ 3፡30 ይከፈታል::

7 የጨረታው አሽናፊ ውጤት እንደተገለፀ በአምስት/5/ ቀን ውስጥ ውል ማሰር ይኖርበታል:: የጨረታው አሸናፊ የጨረታው ውጤት እንደተገለፀ የመልካም ስራ አፈፃፀም ከጠቅላላ ዋጋ 10% cpo ወይም Unconditional Bank Grantee ማስያዝ ይኖርበታል::

8 ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

9 ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0342-40-00-14 ወይም 0344-410396 መቐለ ዋና ቢሮ በመደወል ማረጋገጥ የምትችሉ መሆናችሁን እንገልፃለን::

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo