በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜን ዕዝ 5ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር መምሪያ በ2011 በጀት ዓመት ለክ/ጦራችን ሥራ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ዓይነት ቋሚና አላቂ የቢሮ የጽሕፈት መሣሪያ ዕቃዎች፣የተለያዩ ዓይነት አላቂ የፅዳት ዕቃዎች፣የተለያዩ ዓይነት የቀላል ተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች የኮምፒዩተር ዕቃዎችና ጥገና፣ የእጅና የእግር ኳስን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

በሀገር መከላከያ ሚኒስትር የሰ/ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ
  • ቋሚና አላቂ የቢሮ የጽሕፈት መሣሪያ ዕቃዎች፣
  • የተለያዩ ዓይነት አላቂ የፅዳት ዕቃዎች፣
  • የተለያዩ ዓይነት የቀላል ተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች
  • የኮምፒዩተር ዕቃዎችና ጥገና፣
  • የእጅና የእግርኳስን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች በሙሉ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላችሁ  የዘመኑን ግብር የከፈላችሁ መሆናችሁን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ  የምትችሉ እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆንና አለባችሁ፡፡ተጫራቾች የማስረጃችሁን ፎቶ ኮፒ በማቅረብ የዕቃዎችን  ዝርዝር የያዙ ሰነድ የማይመለስ ብር 50.00 (ሃምሳ ብር) በመክፈል ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት በ33ኛ ክ/ጦር ጎንደር  አዘዞ ወ/ዊ ካምፕ ግዥ ከፍል ቢሮ እየቀረባችሁ መግዛት ትችላላችሁ።ተጫራቾች ለተሸናፊው ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ CPO ወይም በካሸ  ማስያዝ ይኖርባችኋል፡፡ተጫራቾች የእያንዳንዱ የዕቃ ዋጋ በሰም በታሸገ  ኤንቨሎፕ በማድረግ እስከ ሚያዝያ 28 ቀን 2011 ዓ/ም ከቀኑ 8፡00  ሰዓት ድረስ ሰነዱን ከገዙበት ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባችሁ፡፡ጨረታው በዕለቱ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 8፡15 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኘበት የ33ኛ ክ/ጦር ወ/ዊ መዝናኛ ክበብ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው:: 

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0913133315 ወይም 0915279453 ደውለው ማረጋገጥ ይችላሉ፡፡ 

የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜን ዕዝ 

የ5ኛ ሜ/ድ ክ/ጦር መምሪያ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo