መስሪያ ቤታችን መቐለ ሆስፒታል የተለያዩ የህክምና መገልገያ እቃዎች ከህጋውያን ነጋዴዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ስለዚህ መስፈርቱን የምታሟሉ ህጋውያን ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ይጋብዛል፡፡

መቐለ ሆስፒታል

መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች

1. የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN NO/ እንዲሁም የታደሰ የኣቅራቢዎች ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፤

2.የ 6 ወር ግብር የከፈሉበት ማስረጃ እና የታደሰ ብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፤

3. የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ /CPO/ ብር 100,000 ማስያዝ የሚችሉ፤

4.ተወዳዳሪዎች የጨረታውን ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ዶክሜንት አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ ዶክሜንት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕበተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በስራ ሰአት የግዥ ንኡስ ስራ ሂደት ማስገባት አለባቸው፤

5. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታወጀበት ቀን ጀምሮ ለ30 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሆኖ የመከፈቻ ቀን እና ሰዓት እንዲሁምሌሎች አስፈላጊ የሆኑ መመሪያዎች በሙሉ በሚሸጠው ጨረታ ሰነድ መመልከት ይቻላል፤

6. ተወዳዳሪዎች በተሰጠው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት የመወዳደሪያ ዋጋቸውን መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡

7. ተወዳዳሪዎች የሚያስገቡት ዋጋ የትራንስፖርት እንዲሁም ሌሎች ወጪዎች ያካተተ መሆን አለበት፡፡ ካልሆን እንዳካተተ ይቅጠራል፤

8. ተወዳዳሪዎች አሸናፊ ሆነው ከተገኙ ውል ከገቡበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር ያሸነፉት ንብረት በ90 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማቅረብይጠበቅባቸዋል፡፡

10. የጨረታ ሰነድ ዋጋ የማይመለስ ብር 100.00 /እንድ መቶ ብር/ ከፍለው ከመስሪያ ቤታችን የግዥ ስራ ሂደት 4ኛ ፎቅ በስራ ሰአትመግዛት ይችላሉ፤

11. ቢሮው የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው እንዲሁም 20% መጨመር አልያምመቀነስ ይችላል፤

12. ማንኛውም ግልፅ ያልሆነ ጥያቄ ካላችሁ ጨረታ ሰነድ የሚከፈትበት ቀን ከመድረሱ ከ5 ቀናት በፊት ጥያቄያችሁን በፅሑፍ ማቅረብይጠበቅባችኋል፡፡

12. ዋጋ ፀንቶ የሚቆይበት (BID VALIDITY DATE) 60 ቀናት ይሆናል፤

13. በእያንዳንዱ ንብረት አሸናፊ ይለያል በድምር ወይም በጠቅላላ አሸናፊ አይደረግም፤

ለበለጠ መረጃ በትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ

ለመቐለ ሆስፒታል በስልክ ቁጥር 09-32-06-35-04 ደውለው

መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo