ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ/የተ/የግ ማህበር መቐለ ዋና መስርያ ቤት የሚገኘው የትሬንግ ሴንተር ህንፃ የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::

ትራንስ ኢትዮጽያ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

ትራንስ ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር

የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ሰነድ ቁጥር LT 008/2018/2019

ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ/የተ/የግ ማህበር መቐለ ዋና መስርያ ቤት የሚገኘው የትሬንግ ሴንተር ህንፃ የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎች በጨረታአወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::

ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መስፈርቶች በማሟላት በጨረታው እድትሳተፉ ይጋብዛል::

1. ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ የ2011 ዓ.ም ያላቸውና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው (የማስረጃው ፎቶ ኮፒ ማያያዝያስፈልጋል)

2. ተጫራቾች በዚሁ ስራ የተስማሩ መሆናቸው ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው

3. ተጫራቾች የጨረታ ዋጋ ሲያስገቡ በጨረታ ዶኩሜነቱ በተቀመጠው ስፔስፊኬሽን መሰረት መሆን አለበት:: እንዲሁም ግዢሲፈፀምላቸው ሕጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል::

4. የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 30 ስላሳ ብር/ በመክፈል ከሚያዝያ 07 ቀን 2011 ዓም ጀምሮ ከአዲስ አበባላይዘን ኦፊስ ግዢ ማስተባበሪያ ትራንስ ህንፃ እና መቀሌ ከሚገኘው የግዢና ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡

5. የጨረታ ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 2% ቫትን ጨምር በሰፕኦ (CPO) ወይም በአንኮንድሽናል ባንክ ጋራንቲ መልክ ማስያዝይኖርባቸዋል።

6. ተጫራቾች ላሽነፉት ዕቃዎች ክፍያ የሚፈፀምላቸው ዕቃዎች ኢንስፔክት ተደርገው የገቢ ደረሰኝ ከተቆረጠላቸው በኃላ መሆኑተጫራቾች አስቀድመወዙ ማወቅ አለባቸው::

7. ተጫራቾች በተሰጣቸው ሰነድ ውስጥ ብቻ ዋጋቸውን ሞልተው በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ እስከ ሚያዝያ 25 ቀን 2011 ዓ.ምከጥዋቱ 4፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ በአዲስ አበባ ላይዘን ኦፊስ ግዢ ማስተባበሪያ ቢሮ/ትራንስ ህንፃ ወይም በመቀሌ በሚገኘውየግዢ ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።

8. ጨረታው በዚሁ ቀን ማለትም ሚያዝያ 25 ቀን 2011 ዓም ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውበተገኙበት በአዲስ አበባ ላይዘን ኦፊስ ግዢ ማስተባበሪያ ቢሮትራበ ህዝ እና በመቀሌ ዝ፡ ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮበተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል:: በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጫረታው በተጠቀሰው ሰዓትይከፈታል::

9. ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

10. ተጨማሪ ማብራርያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 34-441 64 39 / 034-440 82 05 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo