በትግራይ ክልል የኮንስትራክሽን መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ የህንፃ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ዳይሬክቶሬት በ2011 በጀት ዓመት በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ኮረም ከተማ የሚገነባ የአትሌቲክስ ስፖርት ፊልድ ፕሮጀክት ግንባታ ለማካሄድ በደረጃ BC-5/GC-6 እና ከዛ በላይ ፈቃድ ላላቸው ስራ ተቋራጮች አጫርቶ ማሰራት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድን ትራንስፖርትን ቢሮ
  • የ2011 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ ፣ የኮንስትራክሽን ፍቃድ የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፍኬት ፣ የቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ፣ ያለፈው ወር የቫት ዲክላሬሽን እና የቲን ምዝገባ ሰርተፍኬት ማስረጃዎችን ማቅረብ የሚችሉ።
  • የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) በህግ እውቅና ካለው ባንክ በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና (Un conditional bank guarantee) ወይም የገንዘብ ክፍያ ማዘዣ (CPO) መሰረት ብር 400,000.00 (አራት መቶ ሺ ብር) ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • መስፈርቱን ለሚያሟሉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 30 (ሰላሳ) ቀናት ውስጥ ለግንባታው ሰነድ መግዣ የማይመለስ ብር 300 (ሦስት መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ ወደ ትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ የህንፃ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 191 በአካል በመቅረብ ወይም በ0344408775 የስልክ መስመር በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
  • ቢሮው ጨረታውን በከፊል ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።

በትግራይ ክልል የኮንስትራክሽን መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ የህንፃ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ዳይሬክቶሬት

ዳይሬክተር /መቐለ/

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo