የሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም /መቐለ/ Red Ash፣ ኣሸዋ፣ ጠጠርØ2፣ የተለያዩ መጠን ያላቸው ቴንዲኖ፣ የተለያዩ መጠን ያላቸው ሚስማር፣ soft wire 1.5 mm፣ Mold oil ጥቁር ድንጋይ የፎርም ወርክ ጣውላ (wooden board with 4m length 30cm and 5mm thickness formwork) እና የተለያዩ መጠን ያላቸው ባህርዛፍ ግዥ በጨረታ ኣወዳድሮ መግዛት ስለሚፈልግ በዘርፉ ፍቃድ ያላችሁ ኣቅራቢዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።

የሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም

ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው ነገሮች

1 የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ ግብር የከፈሉና እና የቫት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤

2 ተጫራቾች ከ 26/07/2011ዓ/ም እስከ 10/08/2011ዓ/ም ጅምሮ ክፍል 3 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 403 በመምጣት የማይመለስ ብር /ሃምሳ ብር/ 50.00 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡ከዚህ በኃላ የሚቀርብ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡

3 ጨረታዉ ፍላጎት ያላቸዉ ተጫረቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት 10/08/2011 ዓ/ም ከቀኑ 8:15 ይከፈታል።

4 ተጫራቾች ለRed Ash 70000.00 ሺ ብር፣ ለኣሸዋ፣ ጠጠርØ2 3000.00 ሺ ብር፣ለ ጥቁር ድንጋይ የፎርም ወርክ ጣውላ 3000.00 ሺ ብር፣የተለያዩ መጠን ያላቸው ቴንዲኖ ሚስማር soft wire 1.5 mm፣ Mold oil 10000.00 ሺ ብር፣ የተለያዩ መጠን ያላቸው ባህርዛፍ 5000.00 ሺ ብር፣ በባንከ የተረጋገጠ ቼክ ወይም ስፒኦ ማስያዝ አለበት፤

5 አሸናፊዉ የሚሆኑ ተጫራቾች በራሱ ትራንስፖርት ኣገልግሎት ኣጓጉዞ ቃላሚኖ ት/ቤት ኣካባቢ በሚገኘው የኢትዮ ቴሌኮም ግቢ ማስረከብ ይኖርበታል፡፡

6 መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፤

ተጫራቾች ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0344-413134 መደወል ይችላሉ፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo