ቃሊቲ ኮንስትራክሽን እቃዎች ማምረቻ ፋብሪካ በኣፋር ክልል ኣህመድ ኢላ ኣርታኤለ መንገድ የኮንክሪት ኣቅርቦት ፕሮጅክት የፕሮጀክቱ የሰርቪስ ኣገልግሎት የሚሰጥ ለ15 ሰው በላይ የመያዝ ኣቅም ያለው ሚኒባስ መኪና በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

ቃሊቲ ኮንስትራክሽን እቃዎች ማምረቻ ፋብሪካ

1 ተጫራቾች ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑ ግብር የከፈሉ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ኣለባቸው፤

2 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት መቀሌ በሚገኝ የመከለከያ ኮንስትራክሽን የመቀለ ባለ ሶስት ኮከብ ሆቴል ፕሮጀክት ቢሮ በመቅረብ መግዛት ይቻላል፡፡

3 ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ እስክ መጋቢት 30/2011ዓ/ም ­ጧት 4፡00 ሰዓት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

4 ጨረታው መጋቢት 30/2011ዓ/ም ከቀኑ 9፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይ ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቀሌ በሚገኘው የመከላከያ ኮንስትራክሽን ባለ ሶስት ኮከብ ሆቴል ኣዳራሽ ይከፈታል፡፡

5 ፕሮጀክቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስ.ቁጥር 0912-916819/0911-765973 መደወል ይቻላል፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo