የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የማር ማቀነባበሪያ ማሽን፣የእንስሳት ህክምና መገልገያ እቃዎች፣አነስተኛ የእጅ እርሻ መሳሪያዎችና የመስኖ ውሃ ፍሰት መቆጣጠሪያ መሳርያ ፓርሻል ፍሉም (Parshall flume) ፣የማንጎ ፍሬ ዘር፣ የኣይቲ እቃዎች (IT Equipments ) በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ
  • የማር ማቀነባበሪያ ማሽን
  • የእንስሳት ህክምና መገልገያ እቃዎች
  •  አነስተኛ የእጅ እርሻ መሳሪያዎችና የመስኖ ውሃ ፍሰት መቆጣጠሪያ መሳርያ ፓርሻል ፍሉም (Parshall flume)
  • የማንጎ ፍሬ ዘር
  •  የኣይቲ እቃዎች (IT Equipments )

1 በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ፡፡ በመሆኑም በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላችሁአቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን የተዘጋጀው የጨረታ ዶክመንት የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር /በመክፈል  መጋቢት 16 ቀን 2011 ዓ/ም ጀምሮ ከቢሮአችን የዕቃ ግዢ ንኡስ ሥራ ሂደት በስራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድየምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ፣ በጨረታው ላይ ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ይጠበቅባችኋል፣

2 ለዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርቲፊኬት ፣የቫት ሰርቲፊኬትና ያለፈው ወር ሻት ሪፖርት የተደረገበት ማስረጃ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN/፣ ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት፣
3 ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው፣

4 የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በእያንዳንዱ ጨረታ ዶክመንት ላይ የተገለፀው መጠን በቢሯችን ስም በሲፒኦ አሰርተው ጨረታውከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣

5 ቢሯችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 15% ለመቀነስ ወይም ለመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፣

6 ጨረታው ሚያዝያ 15/2011ዓ/ም ከጧቱ በ3.30 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ዕለት በ4.00 ሰዓት ላይ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች
7 ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮኣችን ዕቃ ግዢ ንኡስ ስራ ሂደት ይከፈታል፤

8 ቢሯችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፣

9 ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 0344-403663 ፣ 0344-404723 ወይም በፋክስ ቁጥር 0344-409971 መጠየቅ ይቻላል፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo