የትግራይ ልማት ማህበር ዴስክቶፕ ኮምፒተር፣ ሞኒተር፣ኪቦርድ፣ማውዝ፣ ስተፕላይዘር፣ ዲቫይደር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ልምዓት ማሕበር
  • · 1-ዴስክቶፕ ኮምፒተር ብዛት 100 ፣
  • · 2-ቲንክሌንት ብዛት 2300፣
  • · 3-ሞኒተር ብዛት 2300፣
  • · 4- ኪቦርድ ብዛት 2300 ፣
  • · 5-ማውዝ ብዛት 2300 ፣
  • · 6- ስተፕላይዘር ብዛት 100፣
  • · 7- ዲቫይደር ብዛት 1200 / እና ሌሎች ተጨማሪ የኤሌክትሮኒክስ አክሰሰሪዎች

1 የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፣

2 የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /Tin Number/ ሰርትፍኬትና የመጨረሻ ወር የቫት ዲክላሬሽን የሚያቀርቡ

3 የዘመኑ የታደሰ የአቅራቢነት የምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፣

4 የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣

5 ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣

6 ተጫራቾች አሸናፊ ሁነው ሲገኙ ውሉ ከታሰረበት በ60 ተከታታይ ቀናት የኤሌክትሮኒክ እቃዎቹ ማቅረብ የሚችሉ

7 ተጫራቾች 100,000.00 የኢትዮጵያ ብር የጨረታ ማስከበርያ በሲፒኦ ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

8 ተጫራቾች የጨረታው ሰነደቻቸውን በሁለት የተለያዩ ኤንቨሎፖች የቴክኒካል እና ፋይናንሻል ኦርጅናል ሰነዶች ለያይተው በማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።በተጨማሪም ከቴክኒክ እና ከፋይናንሻል ሰነድ አንድ አንድ ኮፒ በማሸግ ፌርማና የድርጅቱ ማሕተም በማሳረፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል ፣

9 የጨረታው ሰነድ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ ብር 100 (መቶ ብር) በመክፈል መቐለ በሚገኘው ትግራይ ልማት ማህበር ፅ/ቤት ከቢሮ ቁጥር 430 ወይም አዲስ አበባ ቦሌ መድሃኒ አለም ፊትለፊት 7 ፎቅ የሚገኘው ህድሞና ህንፃ ቢሮ ቁጥር 12 መውሰድ ይችላሉ፣

10 ይህ ጨረታ በማስታወቅያ በወጣ በ16ኛው በ8:30 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ 9:00 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባሉበት በትግራይ ልማት ማሕበር መቐለ በሚገኘው ዋና ፅ/ቤት ይከፈታል፣

11 የጨረታ መክፈቻው ቀን የበአል ቀን ወይም ቅዳሜና እሁድ ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፣

12 አሸናፊዎች ያሸነፉት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች መቐለ በሚገኘው የትግራይ ልማት ማሕበር ዋና ፅ/ቤት ማድረስ ይጠበቅባቸዋል

13 አሰሪው ፅ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፤-0344406944 መጠየቅ ይቻላል

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo