የመቀሌ ከተማ ዕቅደና ፋይናንስ ጽ/ቤት ለመቀሌ ከተማ ጽሕፈት ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የዕቃ ማቅረብ እና የኔት ወርክ ዝርጋታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የመቐለ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ጽህፈት ቤት
  1. ማንኛወም በዘርፉ የተሰማራና ብቃት ያለው የንግድ ድርጅት ከላይ የተዘረዘሩትን ዕቃዎች ለማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል፡፡
  2. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ከ9/7/2011 ዓ.ም ጀምሮ የማይመለስ ብር 50.00/ ሃምሳ ብር/ ከመቀሌ ከተማ ኣግአዚ ኦፕሬሽን ሕንፃ በሚገኘው የመቀሌ ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽ/ቤት 1ኛ ፎቅ ቁጥር 034 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ጨረታ የዘመኑ ግብር የከፈሉበት የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የቅርብ ወር ቫት ዲከለሬሽን የአቅራቢነት ምዝገባ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ጨረታ ማስከበሪያ የኢንተርኔት ዝርጋታ 100,000.00 በCPO ወይም በባንከ የተረጋገጠ በሁኔታ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ወይም ካሽ ወይም በባንክ የተረጋገጠ ቼክ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ለቴክኒካል አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ እንዲሁም ለፋይናንሻል ''አንድ'' ኦርጅናል እና "አንድ ኮፒ፣ በታሸገ ፖስታ ለየብቻቸው በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ጨረታ የሚከፈትበት ቀን 24/7/2011 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
  7. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸው ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
  8. ጨረታ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሰው ቀን በጽ/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 034 ይከፈታል፡፡
  9. ተጫራቾች ስለጨረታው ማብራሪያ ከፈለጉ ስልክ ቁጥር፡- 0342408757/ 408501 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  10. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የመቀሌ ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo