የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የስደተኞች ተፅእኖ ምላሽ ልማት ፕሮጀክት (DRDIP) የኤሌክትሪክ ጀነሬተሮች፣ ኤሌክትሪካል ሆሪዞንታል ሳርፌስ ፓምፕና ስሞል ዲዝል ኢንጂን ድሪቭን ዋተር ፓምፕስ በግልፅ ጨረታ(NCB)አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ

ሎት 1
የኤሌክትሪክ ጀነሬተሮች፣
ኤሌክትሪካል ሆሪዞንታል ሳርፌስ ፓምፕና ስሞል ዲዝል ኢንጂን ድሪቭን ዋተር ፓምፕስ በግልፅ ጨረታ(NCB) አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፤

1 በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፡ የተዘጋጀው የጨረታ ዶክመንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ከ10/07/11 ዓ.ም ጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን በጨረታውለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል፡፡
2 የዘመኑ የታደሰ ን ግድ ፈቃድ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፍኬት የVAT ሰርተፍኬት፡ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN ) እናያለፈው ወር ቫት (VAT ) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት፡፡

3 ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው።
4 የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond ) በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ በ CPO አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱበፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል
5 ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 15% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
6 ጨረታው 10/08/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ይከፈታል፡፡

7 ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 0344403663 / 0344404346 ወይም በፋክስ ቁጥር 0344409971/ 0344403663 መጠየቅ ይቻላል፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo