የትግራይ ልማት ማሕበር በቆላ ተምቤን ወረዳ የትምህርትና የጤና ተቋሞችን በስድስት ሎቶች በመከፋፈል ማሰራት ይፈልጋል

የትግራይ ልምዓት ማሕበር

1. ደረጃቸው GC/BC-5 ከዝያ በላይ የሁኑ የ2011 ዓ.ም የኮንስተራክሽን ፍቃዳቸውና የንግድ ሥራ ፈቃዳቸው ያሳደሱ፣ በኮንስትራክሽን ኣቅራቢነትና ሰርትፍኬት ያላቸው፣ የቫት ሰርትፍኬት፣ የቲን ሰርትፍኬትና የመጨረሻ ወር የቫት ዲክላሬሽን የሚያቀርቡ፣ ቴክኒካል ዶክመንት ጋር ተያይዞ ካልቀረበ ከውድድር ውጭ ይሆናሉ

2. የጨረታው ማስከበርያ ዋስትና በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው የታወቁ ባንኮች 50,000.00 (አምሳ ሺ ብር) በሲፒኦ ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣

3. ተጫራቾች ለሚሰሩት የህንፃ ፕሮጀክት ሳይት ከተረከቡበት ቀን ጀምሮ በ210/ ሁለት መቶ አስር ተከታታይ ቀናት ኣጠናቆ ማስረከብ የሚችሉ፣

4. የጨረታው ዶክመንት ከ02/07/2011 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 27/07/2011 ዓ/ም ኣስፈላጊዉን ዶክመንት በመያዝ የማይመለስ ብር 500 (ኣምስት መቶ ብር) በመክፈል ከትግራይ ልማት ማህበር ዋና ፅ/ቤት ቢሮ ቁጥር 435 መውሰድ ይችላሉ፣

5. የጨረታው ሰነድ በተጫራቾች መመርያ መሰረት ተሞልቶ፣ ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዶክመንቶች ኦርጅናሉና ሁለት ፎቶ ኮፒዎች፣ ሲፒኦ ለየብቻቸው በፖስታ ታሽጎው በአንድ ትልቅ ፖስታ ውስጥ ተከተውና በላይ ላይ ለሚጫረቱት ፕሮጀክትIሎት ስም በሚታይ ቀለም ፅፈው በሁሉም ዶክመንት (ኣጠቃላይ ላይ ተፈርሞበትና ህጋዊ የሆነ ማህተም በመምታት እስከ 27/07/2011 ዓ/ም ጧት 3:30 ሰዓት በትግራይ ልማት ማህበር ዋናው ፅ/ቤት ለዚሁ አገልግሎት የተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣

6. ኣንድ ተጫራች ከኣንድ ሎት በላይ ዶክመንት መግዛትም ሆነ መወዳደር ኣይችልም፣ ከትልማ. ህንፃ ፕሮጀክት ወስዶ ይህ የጨረታ ሰነድ ኣየር ላይ እስከዋለበት ቀን ድረስ ፊዚካል ኣፈፃፀሙ እንዲሁም ከ70% በታች የሆነ ፕሮጀክት ያለው ተጫራች ጨረታ ዶክመንት መግዛትም ሆነ መወዳደር ኣይችልም፣

7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባሉበት 27/07/2011 ዓ/ም ከጧቱ 4:00 ሰዓት በተጠቀሰው ቦታ ይከፈታል፣

8. ኣሰሪው ፅ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው ኣይገደድም፡፡

9. ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር ፧ -034-440-68-40 መጠየቅ ይቻላል::

የትግራይ ልማት ማሕበር

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo