ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የፅህፈት መሳርያ፣ህንፃ መሳርያ ፣ደንብ ልብስ፣ የኤሌክትሪክ እቃዎች ኣወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ
  1.  በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱንም በዘመኑ የታደሰ ለመሆነ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡

  2. በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል፡፡

  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ምዝገባ ሰርተፊኬት፡፡

  4. ተጫራቹ (Tin) ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል፡፡

  5. ለጨረታ ማስከበሪያ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስም እንደሚከተለው ማስያዝ የሚችል ይሆናል።

    *ሎት 1 የፅህፈት መሳርያ:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

    *ሎት 2 ህንፃ መሳርያ:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

    *ሎት 3 ደንብ ልብስ:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

    *ሎት 4 የኤሌክትሪክ እቃዎች - 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

  6. ተጫራቾች የማቅረቢያ /የአቅራቢ ሰርተፍኬት የተመዘገቡ መሆን አለባቸው።

  7. ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል በዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ከዓዲግደራትዩኒቨርሲቲ ግዥና ንብረት ኣስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት ብሎክ 13 ቁጥር 7 መውሰድ የሚችል ሲሆን ዋጋው መቅረብ ያለበትደግሞ ከዩኒቨርሲቲው የሚሸጥ ኦርጅናል የመምርያ ሰነድ ማህተም ያለበት ዶክሜንት ማህተም የተጫራቹ በማድረግ ስርዝ ድልዝየሌለው ዋጋ ብቻ ነው።

  8. የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚሸጥ ይሆናል።

  9. ጨረታው ሳጥን የሚከፈትበት ቀን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመጨረሻ 16ኛው የስራ ቀን 4:00 ሰዓት ተዘግቶበ4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት በግልፅ ይከፈታል።

  10. ዝርዝር ስፔስፊኬሽን በድህረ ገፅ http://www.adu.edu.et ማግኘት ይቻላል።

  11. ዩኒቨርሲቲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

ለበለጠ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር፡- 034 445 23 18 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo