በትግራይ ክልል የኮንስትራክሽን መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ የህንፃ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ዳይሬክቶሬት በ2011 በጀት ዓመት ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ቦታዎች የህንፃ ግንባታ በየፕሮጀክቱ በተገለፀው ደረጃ መሰረት አጫርቶ ማሰራት ይፈልጋል።

የትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ

1. በመቐለ ከተማ የመለስ አካዳሚ ሊደርሺፕ የዶርሚተሪ ብሎክ G+4 ህንፃ ግንባታ 6ተኛ ዙር በደረጃ BC-4/GC-5 እና ከዛ በላይ የስራ ተቋራጮች

2. በመቐለ ከተማ የአትክልትና ፍራፍሬ ገበያ ማእከል ከAGP-II በተገኘ በጀት በደረጃ BC-4/GC5 እና ከዛ በላይ የስራ ተቋራጮች

3. በዓድዋ ከተማ የገጠር ዓድዋ አስተዳደር ህንፃ ግንባታ ለማካሄድ በደረጃ BC-5/GC-5 እና ከዛ በላይ የስራ ተቋራጮች

4. በሽረ እንዳስላሴ ከተማ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ህንፃ ግንባታ ከቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው ፋውንዴሽን በተገፕ በጀት በደረጃ BC-5/GC-6 እና ከዛ በላይ የስራ ተቋራጮች

5. በሽረ እንዳስላሴ ከተማ ወተትና የወተት ተዋፅኦ ህንፃ ግንባታ ለማካሄድ ከAGP-II በተገኘ በጀት በደረጃ BC-6/GC-6 እና ከዛ በላይ የስራ ተቋራጮች

6. በፀለምቲ እና በወልቃይት ወረዳዎች የሃምሳ ሺ ኩንታል ስቶር ህንፃ ግንባታ ለማካሄድ ከ AGP-II በተገኘው በጀት በደረጃ BC-6/GC-6 እና ከዛ በላይ የስራ ተቋራጮች ማሰራት ይፈልጋል።

በዚህም መሰረት ተጫራቾች በዚህ ጨረታ መሳተፍ ለሚፈልጉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው።

*የ2011 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ ፣ የኮንስትራክሽን ፍቃድ፣ የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፍኬት ፣ የቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ፣ ያለፈው ወር የቫት ዲክላሬሽን እና የቲን ምዝገባ ሰርተፍኬት ማስረጃዎችን ማቅረብ የሚችሉ።

*የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) በህግ እውቅና ካለው ባንክ በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና (un Conditional bank guarantee) ወይም የገንዘብ ክፍያ ማዘዣ (CPO) መሰረት ከተ/ቁጥር 1 እስከ ተ/ቁጥር 4 ያሉ ፕሮጀክቶች ለእያንዳንዱ ብር 400,000 (አራት መቶ ሺ ብር) ተ/ቁጥር 5 እና 6 130,000 (አንድ መቶ ሰላሳ ሺ) ብር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

• ከላይ ለተዘረዘሩት የህንፃ ግንባታዎች መስፈርቶቹን ለሚያሟሉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 30 (ሰላሳ) ቀናት ውስጥ ለያንዳንዱ ህንፃ ግንባታ የማይመለስ ብር በመክፈል ከተ/ቁጥር 1 እስከ ተ/ቁጥር 4 ብር 500 (አምስት መቶ) ብር ተ/ቁጥር 5 እና 6 ብር 300 (ሦስት መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።

• ለተጨማሪ ማብራሪያ ወደ ትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ የህንፃ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 191 በአካል በመቅረብ ወይም በ 034 440 8775 የስልክ መስመር በመደወል መጠየቅ ይቻላል።

*ቢሮው ጨረታውን በከፊል ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።

በትግራይ ክልል የኮንስትራክሽን መንገድና

ትራንስፖርት ቢሮ የህንፃ

ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ዳይሬክቶሬት

ዳይሬክተር መቐለ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo