የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ያለቀለት የተፈጨ ሽሮ ፣ሩዝ፣የኤሌክትሪክ ዕቃዎች ፣የፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገድ አገልግሎት፣ኮምፒውተር እና ተዛማጅ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

መቐለ ዩንቨርስቲ
  1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱንም በዘመኑ የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  2. በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን እና መስፈርት መሰረት ማቅረብ የሚችል።
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል
  4. መለያ

    የጨረታው ዓይነት

    የጨረታ ማስከበሪያ

    ደረጃ

    Lot 1

    ያለቀለት የተፈጨ ሽሮ

    100,000.00

    Lot 2

    ሩዝ

    100,000.00

    Lot 3

    የኤሌክትሪክ ዕቃዎች

    50,000.00

    Lot 4

    የፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገድ አገልግሎት

    100,000.00

    Lot 5

    ኮምፒውተር እና ተዛማጅ  ዕቃዎች

    50,000.00

     በባንክ የተመረከረለት CPO /ሲፒኦ/ወይም የባንክ ዋስትና በመቐለ ዩኒቨርስቲ ስም ማስያዝ የሚችሉ፡- 
  5. ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ለዚሁ የተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላል፤
  6. ማንኛውም ተጫራች ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከመቐሌ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳ/ጽ/ቤት መውሰድ ይችላል፡፡ 
  7. ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን 3፡30  ሰዓት ድረስ ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን የመወዳደሪያ ሰነዳቸው ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
  8. ጨረታው ከወጣበት በ16ኛው ቀን ጠዋት 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በቀኑ ልክ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልፅ ይከፈታል።
  9. በጨረታው አሸንፎ በወቅቱ ውል ለማያስር የጨረታ አሸናፊ ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ (CPO) አይመለስለትም፡፡
  10. ዮኒቨርሲቲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ ማብራሪያ፡-

የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር C21-201

  ስልክ ቁጥር፡-  0344 41 47 84/09 14 72 74 48፣ ፖ.ሳ.ቁ 231

ዋና ግቢ፣ መቐለ ዩኒቨርሲቲ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo