የሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም የተለያዩ ዕቃዎች ይዞ የመጣ የጣዉላ ሳጥን፣ ያገለገለ ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ መሸጥ ይፈልጋል።

የሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም

ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው ነገሮች

1 ተጫራቾች የዘመኑ ግብር የከፈሉና የታደሰ የ2011 ዓ/ም ንግድ ፍቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤

2 ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ በታወቀ በባንከ የተረጋገጠ ቼክ ወይም ስፒኦ ብር 10,000 ማስያዝ አለበት፤

3 ተጫራቾች ከ 28/06/2011ዓ/ም ጅምሮ ሰራተኛ ማህበር ካሸር ክፍል 3 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 306 በመምጣት የማይመለስ ብር /ሃምሳ ኣምስት/ 50.00 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከገዙ በኃላ ለሽያጭ የተዘጋጁ ዕቃዎችን አዋሽ የእህል መጋዘን አጠገብ በሚገኘዉ መጋዝን ዉስጥ ለጨረታ የተዘጋጀዉ ዕቃዎችን በኣካል ቦታዉ ድረስ በመሄድ በስራ ሰዓት ማየት ይጠበቅባቸዋል።

4 ተጫራቾች ዕቃዎቹን የሚገዙበት የጠቅላላ ዋጋ ያለ ቫቱ 15% በማስቀመጥ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ አዘጋጅተዉ ሙሉ አድራሻቸዉ በመግለፅ ሰራተኛ 3 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 306 ያዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን 28/06/2011 ዓ/ም እስከ 7/07/2011 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ከዚህ በኃላ የሚቀርበዉ ማንኛዉም ሰነድ ተቀባይነት የለውም።

5 ጨረታዉ ፍላጎት ያላቸዉ ተጫረቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት 7/07/2011 ዓ/ም ከቀኑ 8:15 በሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም 5 ፎቅ የሚገኘዉ የስብሳባ አዳራሽ ይከፈታል።

6 አሸናፊዉ ተጫራቾች ላሸነፈዉ ዋጋ 15% ቫትን ጨምሮ ገቢ ካደረገ በኃላ በአምስት /5/ የስራ ቀናት ዉስጥ ለጨረታ ተለይቶ የተዘጋጁ አሮጌ ጣዉላ : የጣዉላ ሳጥን : ኬብሉ ና ብረቱ የተፈታ ድራም ብቻ በስራ ሰዓት ማንሳት ኣለባቸው። ሆኖም ግን በጊዜ ገደብ ካላነሱ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ስፒኦ ተደርጎ ሪጅኑ የራሱን አማራጭ ይወስዳል።

7 ዕቃዎቹ በሙሉ ካልሆነ በከፊል መጫረት ኣይችሉም።

8 መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፤

9 አንድ ተጫራች ባቀረበዉ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም

ስልክ ቁጥር 0344-413134

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo