ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ/የተ/የግ ማህበር ባዘጋጀው ስፔስፊኬሽን መሰረት የተለያዩ አላቂ የዎርክ ሾፕ መሳሪያዎች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::

ትራንስ ኢትዮጽያ ኋ/የተ/የግ/ማህበር
  1. በዚህ የስራ መስክ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ 2010 ዓ.ም ያሳደሱና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው(የማስረጃው ፎቶ ኮፒ ማያያዝ ያስፈልጋል)
  2. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ዕቃ የጨረታ ዋጋ ሲያስገቡ በጨረታ ስነዱ በተገለፀው ስፔስፊኬሽን መሆንአለበት፣ከስፔስፊኬሽን ውጭ ያቀረበ ተቀባይነት አይኖረውም፣
  3. ተጫራቾች የጨረታ ዋጋቸው የተጨማሪ እሴት ታክስ የሚጨምርና የማይጨምር መሆኑ ግልፅማስቀመጥ አለባቸው፣ካልገለፁ የጨረታ ዋጋው የተጨማሪ እሴት ታክስ እንዳካተተ ይቆጠራል::
  4. የጨረታው አሸናፊ ጨረታው አሽናፊ መሆኑ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ ያሸነፋቸው ዕቃዎች በ15ተከታታይ ቀናት ውስጥ በራሱ ትራንስፖርት ማስረከብ አለበት::
  5. ተጫራቾች ላሽነፉበት ገንዘብ ክፍያ የሚፈፀምላቸው ያሽነፉት ዕቃ ኢንስፔክት ተደርጎ የገቢ ደረሰኝከተቆረጠለት በኃላ መሆኑ ተጫራቾች አስቀድመው ማወቅ አለባቸው::
  6. የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 50 /አምሳ ብር/ በመክፈል ከመቀሌ ዋና መ/ቤት ከግዢ፣ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮ ወይም ከአዲስ አበባ ላይዘን ኦፊስ ግዢ ማስተባበሪያ ትራንስሕንፃ በስራ ስዓት መውሰድ ይችላሉ፣
  7.  የጨረታ ማስከበሪያ ከጠቅላላ ያስገቡት ዋጋ 2% በትራንስ ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ ማህበር ሰም በሲፕኦ(CPO) መልክ ማስያዝ ይኖርባቸዋል::ሲፒኦ ያላስያዘ ተጫራች ወድያው ከጨረታ ይሰረዛል፤
  8. ተጫራቾች በተሰጣቸው ሰነድ ውስጥ ብቻ ዋጋቸውን ሞልተው በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ እስከ መጋቢት15 ቀን 2011 ዓ.ም በ8፡00 ሰዓት በአዲስ አበባ ላይዘን ኦፊስ ግዢ ማስተባበሪያ በድሉ  ሕንፃ ወይምመቀሌ በሚገኘው የግዢ፣ ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታሳጥን ውስጥ ኦርጅናል እና ፎቶ ኮፒ ለየብቻው ማስገባት አለባቸው::
  9. በጨረታ ሰነዱ የተቀመጠ ቁጥርም በPo ጊዜ ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፣
  10. ጨረታው በዚሁ ቀን ማለትም መጋቢት 15 ቀን 2011 ዓ.ም በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይምህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመቀሌ ዋና መ/ቤት በትንሿ አደራሽ እና በአዲስ አበባ ላይዘን ኦፊስግዢ ማስተባበሪያ ትራንስ ሕንፃ በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታሉ:: በዕለቱ
    ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታ ሰነዱ የተሟላ ከሆነ ይከፈታል::
  11. ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::



ተጨማሪ ማብራርያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 034-441 64 39 /
034-440 82 05 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ::

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo