የመቀሌ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ፅሕፈት ቤት ለጥቃቅን እና ኣነስተኛ ፅ/ቤታችን ኣገልግሎት የሚውሉ የፅሕፈት መሳሪያ በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።ስለዚህ በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከታች የተዘረዘሩ መስፈርቶች የምታሟሉ ከፅ/ቤታችን ሰነድ ጨረታ በመውሰድ እንድትወዳደሩ የጋብዛል።

የመቐለ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ጽህፈት ቤት

1 ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ከ20/06/2011 ጀምሮ የማይመለስ ብር 50.00 (ሃምሳ ብር) በመክፈል ከመቀሌ ከተማ ኣግኣዚ ኦፕሬሽን ህንፃ በሚገኘው የመቀሌ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ፅ/ቤት 1ኛ ፎቅ ቁጥር 034 ማግኘት ይቻላል።

2 ተጫራቾች የዘመኑ ግብር የከፈሉበት የታደሰ የንግድ ፈቃድ ፣የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የቅርብ ወር ቫት ዲክለሬሽን፣ የኣቅራቢነት መለያ ካርድ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።

3 የጨረታ ማስከበሪያ 3000.00/ሶስት ሺ ብር/፣ በሲፒኦ ወይም በባንክ የተረጋገጠ በሁኔታ ያልተመሰረት የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ የተረጋገጠ ቼክ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።

4 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸዉን በሁለት ፖስታ ኣንድ ኦርጅናል እና ኣንድ ኮፒ ለየብቻቸዉ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

5 ጨረታ የሚከፈትበት ቀን 05/07/2011ዓ/ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 9:00 ሰዓት ይከፈታል።

6 የተዘጋጀው የጨረታ መወዳደሪያ ሰነድ በከፊል ማቅረብ ፈፅሞ የተከለከለ ነው፤

7 ይህ ጨረታ የሚቆይበት ግዜ /validity period/ ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ቢያንስ ለ60 የስራ ቀናት የፀና ይሆናል፤

8 ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉ በከፈል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

9 ኣድራሻችን በመቐሌ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ፅ/ቤት በዓይደር ክፍለ ከተማ እንዳማርያም ጉግሳ ቤተክርስትያን አጠገብ ኣግኣዚ ኦፕሬሽን ህንፃ ስልክ ቁጥር 0344-406839/0348-990089/ 0344-408501

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo