ኢማጂን ዋን ዴይ ኢንተርናሽናል ኦርጋናይዜሽን /Imagine 1 day/ የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ የውጭ በጎ ኣድራጎት ድርጅት በትግራይ እና በኦርሚያ ክልል በትምህርት ጥራት ማሻሻል ስራ ላይ የበኩሉን ኣስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል፤ በመሆኑም ድርጅቱ በትግራይ ክልል በደቡባዊ እና በምስራቃዊ ዞን የውሃ ቁፋሮ ለመስራት ከክልሉ መንግስታዊ በገባው የፕሮጀክት ውል መሰረት፤

ኢማጅን ዋን ደይ

1 በእምባ ኣላጀ ወረዳ ኣፀላ ቀበሌ ሜዳ ኣፀላ ኣንደኛ ደረጃ ት/ቤት የኣንድ ውሃ ጉድጋድ /Shallow well/

2 በእንዳመሆኒ ወረዳ ህዝባ ተክለሃይማኖት ቀበሌ በኣዲ ኣርባዕተ ኣንደኛ ደረጃ ት/ቤት ኣንድ የውሃ ጉድጋድ /Shallow well/

3 በእንዳመሆኒ ወረዳ መሀን ቀበሌ ዓዲዓጋም ኣንደኛ ደረጃ ት/ቤት የኣንድ ውሃ ጉድጋድ /Shallow well/

4 በእምባኣላጀ ወረዳ ኣምደውሃ ቀበሌ ዘነሽካ ኣንደኛ ደረጃ ት/ቤት የኣንድ ውሃ ጉድጋድ /Shallow well/

5 ክልተ ኣውላዕሎ ወረዳ ደብረወሀቢት ቀበሌ ደብረወሃቢት ኣንደኛ ደረጃ ት/ቤት ጥልቅ ውሃ ጉድጋድ /deep well/

ስለሆነም

1 ተጫራቾች ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን የግብር የከፈሉ እና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ኣለባቸው፤

2 ተጫራቾች በ Per productive ውል መስራት ፍቃደኛ የሆኑ መሆን ኣለባቸው፤

3 ተጫራቾች ስለ ጨረታው የሚገልፀውን ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ እና የታደሰ ንግድ ፍቃዳችሁን ከስራ ልምዳችሁ ጋር በመያዝ ኣዲስ ኣበባ፣ መስቀል ፍላወር፣ ኩባ ኤምባሲ ፊት ለፊት ከሚገኘው የድርጅታችን ዋና መስሪያ ቤት ወይም በትግራይ ክልል መቐለ ሃፀይ ዮሐንስ ሆቴል በስተጀርባ ካለው ፋና ህንፃ ኣራተኛ ፎቅ ከሚገኘው የክልሉ የድርጅቱ ፅሕፈት ቤት ከ 13/06/2011ዓ/ም እስከ 22/06/2011ዓ/ም ባለው የስራ ሰዓት የጨረታ ዶክመንቶችን መግዛት ይችላሉ፤

4 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ባንክ /Bank Guarantee/ ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ለ90 ቀናት የሚቆይ ከሚያቀርቡት ዋጋ ላይ 5% ጨረታው ከመከፈቱ በፊት በስም በታሸገ ኢንቨሎፕ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፤

5 ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ እና ቴክኒካል ፐሮፖዛል በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ የካቲት 22 ቀን 2011ዓ/ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት እስከ 8:00 በኣዲስ ኣበባ፣ መስቀል ፍላወር፣ ኩባ አምባሲ ፊት ለፊት ከሚገኘው የድርጅታችን ዋና መ/ሪያ ቤት ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፤

6 ጨረታ የካቲት 22 ቀን 2011ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኣዲስ ኣበባ፣ መስቀል ፍላወር፣ ኩባ አምባሲ ፊት ለፊት ከሚገኘው የድርጅታችን ዋና መ/ሪያ ቤት ይከፈታል፤

7 ድርጅቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፤

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስ.ቁጥር 011-869 7258/0344-404933

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo