የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትግራይ ክልል ጽ/ቤት ከዚህ በታች በቀረበው ዝርዝር መሰረት concentric service cable ባለ 6mm ከሀገር ዉስጥ አምራቾች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ፡፡

ኢትዮጲያ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት በሰሜን አካባቢ ቢሮ

 ቁጥር

     የዕቃዉ ስምና ይዘት

 መለኪያ

ተፈላጊ ብዛት

  1

Concentric service cable ባለ 6mm2

 ሜትር

800,000

1. መስፈርቱን የሚያሟሉ በዘርፉ የተሰማሩ ብቃት ያላቸው ድርጅቶች መሳተፍ ይችላሉ።

2.ተጫራቶች በዘረፋ የተሰማሩ የዘመኑ ግብር የተከፈለበት የታደስ ንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የ ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሊኖራቸዉ ይገባል፣

3. ተጫራቾች የመንግሥት ድርጅቶች በሚያወጡት ጨረታ ላይ ለመሳተፍ እንዲችሉ በግዥ ኤጀንሲ ዌብሳይት ላይ የተመዘገቡ መሆኑን ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።

4. ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ የጨታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮዘወትር በራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 02 3ኛ ፎቅ በመምጣት የማይመለስ ብር 4,000.00 /አራት ሺ ብር/ በመክፈል መውሰድይችላሉ።

5. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውንና የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ከላይ በተጠቀሰው መሰረት በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ (CPO)ብር 240,000.00 /ሁለት መቶ አርባ ሺ/ በማድረግ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ  ጨረታዉ  ከወጣበት  ቀን  ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ከታች በተገለጸዉ አድራሻ ለዚሁ ሲባል በተዘጋጀው የጨረታ ውስጥ ማስገባት አለባቸው።

6. አድራሻ፦ መቐለ ከተማ ፕላኔት ሆቴል አጠገብ የዛምራ ኮንስትራክሽን ሕንፃ ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትግራይ ክልል ጽ/ቤት 3ኛ ፎቅ ፕሮኪዩርመንት ሎጂስቲክስ፣ ዌር ሃውስ አና ፋሲሊት ቢሮ ቁጥር 01

7. ጨረታው የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት የመጨረሻ ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ላይ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 01 ይከፈታል ። የመክፈቻ ቀን ብሔራዊ በዓል ወይም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ የሚቀጥለው ቀን በተመሳሳ ይ ሰዓት ታሽጐ ይከፈታል።

8. ተጫራቶች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0342406712 መደወል ይችላሉ።

9. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ መሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።



ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo