የመከላኪያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለመቀለ ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ ፕሮጀክት ኣገልግሎት የሚውሉ የእግረኛ መንገድ ታይል የማቅረብና የማንጠፍ /Supply and apply footway cement tiles / ስራ ግዥ ለመፈፀም ህጋዊ ተወዳዳሪዎች በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ በንኡስ ተቃራጭ / sub contract/ ለማሰራት ይፈልጋል::

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ

1 ተጫራቾች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸዉ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸዉ::

2 ተጫራቾች የእግረኛ መንገድ ታይልስ የማንጠፍ ስራ ከ4000 m2 በላይ ስለመስራታቸው የመልካም ሰራ ኣፈፃፀም ውለታ ከክፍያ ሰነድ ጋር የተገናዘበ ማቅረብ የሚችሉ፤

3 ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ከመከፈቱ በፊት 300x300x20mm pre colour chekerd cement tiles የሆነውን የሚያመርቱትን የሚያቀርቡት/ የቸከርድ ታይልስ ናሙና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል::

3 የጨረታ ማስያዣ በ Cpo “unconditional bank guarantee” 50,000.00 ማስያዝ የሚችሉ እና በተጨማሪ ቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤

4 ተጫራች የስራ ዝርዝሩን የሚገልፅ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 200.00 ብር መግዛት ይጠበቅባቸዋል ::

5 ተጫራቾች የሚወዳደሩበት ዋጋ በሰም በታሸገ ፖስታ ከ 13/05/2011 ዓ/ም እስከ 20/05/2011 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ድረስ የቸከርድ ሳምፕል ና ዋጋችሁን ማቅረብ ይኖርባቸዋል::

6 ጨረታው 20/05/2011 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ተዘግቶ ከቀኑ 8:30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በፕሮጀክት ፅ/ቤቱ ይከፈታል::

7 ተጫራቾች የሚሰሩትን የስራ መጠን እንደኣስፈላጊነቱ ሊጨምርም ሊቀንስም ይችላል::

8 ድርጅቱ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ምሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ::

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0914-709013  ኣዋሽ ካምፕ ኣጠገብ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo