በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ዕዝ ጠ/መምሪያ የተለያዩ ተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች፣የተለያዩ የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ ፍላፕ እና ባትሪ፣አቡጀዲድ እና ሻሽ፣የተለያዩ የጋራጅ መርጃ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

መከላለያ ሰሜን ዕዝ ጠ/መምርያ

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 03/2011

በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ዕዝ ጠ/መምሪያ በ2011 በጀት  ዓመት አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተገለጹትንበግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

  • ሎት 1. የተለያዩ ተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች
  • ሎት 2. የተለያዩ የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ ፍላፕ እና ባትሪ
  • ሎት 3. አቡጀዲድ እና ሻሽ
  • ሎት 4. የተለያዩ የጋራጅ መርጃ ዕቃዎች

በዚህም መሠረት በዘርፉ የተሰማሩ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ ሠርተፍኬት፣ የቫት ሠርተፍኬት እና የአቅራቢነትምዝገባ ሠርተፍኬት ያላቸውን ይጋብዛል፡፡ ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መመሪያ እና ዝርዝር ሰነድ የያዘ ለሎት 1 እናሎት 2 ለእያንዳንዳቸው 200.00 (ሁለት መቶ ብር ) ለሎት 3 እና 4 እያንዳንዳቸው 100.00 (አንድ መቶ) ብርበመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት መቀሌ ኩሓ መንገድ እግሪ ወንበር አካባቢ ከሚገኘው የጠቅላይ መምሪያ ግዥ ቡድን ቢሮማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የጨረታ ስነድ በመግዛት በቢሮው ወደተዘጋጀው የጨረታ ሳጥንማስገባት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ጨረታው ጥር 16/2011 ዓም ከጠዋቱ 3:30 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ4:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር :- 0344-41-07-50

በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ዕዝ ጠ/መምሪያ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo