የትግራይ ልማት ማህበር በፈረስ ማይ ከተማ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከል (ምዕራፍ አንድ ህንፃ ፕሮጀክት ) ማሰራት ይፈልጋል፡፡

የትግራይ ልምዓት ማሕበር
  1. ደረጃቸው GC/BC-3 ከዚያ በላይ ፣ የሆኑ  የ2011 ዓ.ም  የኮንስትራክሽን  ፍቃዳቸውንና የንግድ ስራ ፈቃዳቸው ያሳደሱ፣ በኮንስትራክሽን አቅራቢነትና ሰርተፍኬት ያላቸው፣ የቫት ሰርተፍኬት፣ የቲን ሰርተፍኬትና የመጨረሻ ወር የቫት ዲክላሬሽን የሚያቀርቡ ፣  ቴክኒካል  ዶክመንት ጋር ተያይዞ ካልቀረበ ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡
  2. የጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና  በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው የታወቁ ባንኮች 100,000.00 (አንድ መቶ ሺ ብር) በሲፒኦ ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. ተጫራቾች ለሚሰሩት የህንጻ ፕሮጀክት ሳይት ከተረከቡበት ቀን ጀምሮ በ550/አምስት መቶ አምሳተከታታይ ቀናት አጠናቆ ማስረከብ የሚችሉ
  4. የጨረታው ዶክመንት ከ22/04/2011 ዓ.ም  ጀምሮ እስከ 17/05/2011 ዓ.ም አስፈላጊውን ዶክመንት በመያዝ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ከትግራይ ልማት ማህበር ዋና ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 435 መውሰድ ይችላሉ፡፡
  5. የጨረታዉ ሰነድ በተጫራቾች መመርያ መሰረት ተሞልቶ፣ ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዶክምንቶች ኦርጅናሉና ሁለት ፎቶ ኮፒዎች፣ ሲፒኦ ለየብቻቸው በፖስታ ታሽገው በአንድ ትልቅ ፖስታ ውስጥ ተከተውና በላዩ ላይ ለሚጫረቱት ፕሮጀክት ስም በሚታይ ቀለም ጽፈው በሁሉም ዶክመንቶች (አጠቃላይ ላይ ተፈርሞበትና ህጋዊ የሆነ ማህተም በመምታት እስከ 17/05/2011 ዓ.ም ጧት  3፡30 ሰዓት  በትግራይ ልማት ማህበር  ዋናው  ጽ/ቤት  ለዚሁ  የተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ከት.ል.ማ.  ህንፃ ፕሮጀክት  ወስዶ  ይህ  የጨረታ  ሰነድ  አየር  ላይ  እስከዋለበት ቀን ድረስ የፕሮጀክቱ ፊዚካል አፈጻጸሙ ከ70% በታች የሆነ የሥራ ተቋራጭ ጨረታ ዶክመንት መግዛትም ሆነ መወዳደር አይችልም፣
  7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባሉበት 17/05/2011 ዓ.ም ከጧቱ 4፡00 ሰዓት  በተጠቀሰው  ቦታ ይከፈታል፡፡
  8. አሰሪው ጽ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡
  9. ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር -034 440 68 40 መጠየቅ ይቻላል፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo