የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትግራይ ክልል ጽ/ቤት ባለሶስት እና ባለ ሁለት እግር ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ኢትዮጲያ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት በሰሜን አካባቢ ቢሮ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትግራይ ክልል ጽ/ቤት ከዚህ በታች የተገለጹትን ባለሶስት እና ባለ ሁለት እግር ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ሎት

ቁጥር

የተሽከርካሪው አይነት

መለኪያ

ብዛት

የማቅረቢያ ጊዜ

የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ

ሎት 1

1.1

ባለሶስት እግር የጭነት ተሽከርካሪ 395 cc

ቁጥር

30

በ30 /ሰላሳ/ ተከታታይ ቀናቶች

23,400.00

ሎት 2

2.1

ባለ ሁለት እግር ተሽከርካሪ 175 cc

ቁጥር

10

በ30 /ሰላሳ/ ተከታታይ ቀናቶች

20,500.00

2.2

ባለ ሁለት እግር ተሽከርካሪ124.6 cc

ቁጥር

10

  1.  ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩ የዘመኑን ግብር የተከፈለበት የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ፣ የግብር ክፋይ መለያ ቁጥር ሊኖራቸው ይገባል፡፡
  2.  የተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ስዓት ቢሮ ቁጥር 01-3ኛ ፎቅ በመምጣት የማይመለስ ለሎት አንድ ብር 400.00 (አራት መቶ) እንዲሁም ለሎት ሁለት ብር 400.00 (አራት መቶ) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
  3.   ተጫራቾች የመወዲደሪያ ሰነዳቸውንና የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ከላይ በተጠቀሰው መሰረት በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ (ሲፒኦ) ለሎት አንድ ብር 23,400.00/ሃያ ሶስት ሺህ አራት መቶ / እንዲሁም ለሎት ሁለት ብር 20,500.00 (ሃያ ሺህ አምስት መቶ ብር /በማድረግ በስም በታሸገ ኤንቨሎፕ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ከታች በተገለፀው አድራሻ ለዚሁ ሲባል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
  4. አድራሻ፡- መቐለ ከተማ ፕላኔት ሆቴል አጠገብ የዛምራ ኮንስትራክን ህንፃ ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትግራይ ክልል ጽ/ቤት 3ኛ ፎቅ ፕሮኪዩርመንት ሎጂስቲክስ ፣ ዌር ሃውስ እና ፋሲሊቲ ቢሮ ቁጥር 01
  5. ጨረታው የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት የመጨረሻ ቀን ከቀኑ 8:30 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከቀኑ 9:00 ሰዓት ፕሮኪዩርመንት ሎጀስቲክስ ዌር ሃውስ እና ፋሲሊቲ ቢሮ ቁጥር 1 ይከፈታል፡፡ የመክፈቻ ቀን ብሄራዊ በአል ወይም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል
  6.    ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0342406712 መደወል ይችላሉ፡፡
  7. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo