የመቀሌ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ፅሕፈት ቤት ለመቀሌ ከተማ ፅሕፈት ቤቶች ኣገልግሎት የሚውሉ የመኪና ስፔር እና ኤሌክትሮኒክስ በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።ስለዚህ በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከታች የተዘረዘሩ መስፈርቶች የምታሟሉ ከፅ/ቤታችን ሰነድ ጨረታ በመውሰድ እንድትወዳደሩ የጋብዛል።

የመቐለ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ጽህፈት ቤት

ተፈላጊ መስፈርት

1 ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራና ብቃት ያለው የንግድ ድርጅት ከላይ የተዘረዘሩትን እቃዎች ለማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል።

2 ተጫራቾች ለያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ከ17/04/2011 ጀምሮ የማይመለስ ብር 50.00 (ሃምሳ ብር) በመክፈል ከመቀሌ ከተማ ኣግኣዚ ኦፕሬሽን ህንፃ በሚገኘው የመቀሌ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ፅ/ቤት 1ኛ ፎቅ ቁጥር 034 ማግኘት ይቻላል።

3 ተጫራቾች ለያንዳንዱ ጨረታ የዘመኑ ግብር የከፈሉበት የታደሰ የንግድ ፈቃድ ፣የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የቅርብ ወር ቫት ዲክለሬሽን፣ የኣቅራቢነት መለያ ካርድ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ምስክረ ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።

4 የጨረታ ማስከበሪያ የመኪና ስፔር ብር 16,000.00፣ ኤሌክትሮኒክስ ብር 18,000.00 በሲፒኦ ወይም በባንክ የተረጋገጠ በሁኔታ ያልተመሰረት የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ  ወይም በባንክ የተረጋገጠ ቼክ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።

5 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸዉን በሁለት ፖስታ ኣንድ ኦርጅናል እና ኣንድ ኮፒ ለየብቻቸዉ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

6 ጨረታ የሚከፈትበት ቀን 02/05/2011ዓ/ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 9:00 ሰዓት ይከፈታል።

7 ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸው ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ኣለባቸው።

8 ጨረታ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሰ ቀን በፅ/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 034 ይከፈታል።

9 ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉ በከፈል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

10 ኣድራሻችን በመቐሌ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ፅ/ቤት በዓይደር ክፍለ ከተማ እንዳማርያም ጉግሳ ቤተክርስትያን አጠገብ ኣግኣዚ ኦፕሬሽን ህንፃ ስልክ ቁጥር 0342-408757/0344-408501

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo