የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2011 ዓ.ም በጀት አመት የሚያገለግል ሎት አንድ ጀነሬተር ግዢ ሎት ሁለት አልሙኒየም ሳልፌት ሃይድሬት ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት

የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2011 ዓ.ም በጀት አመት የሚያገለግል                                             

  • ሎት አንድ ጀነሬተር ግዢ
  • ሎት ሁለት አልሙኒየም ሳልፌት ሃይድሬት ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታውመሳተፍ ለምትፈልጉ ተጫራቾች ጥሪውን ያቀርባል።
  1. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው።
  2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ።
  3. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ/ በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣትየጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ።
  4. ጨረታ ዶክሜንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 4፡00ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ።
  5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  6. ሁሉም ተጫራቾች ለሎት አንድ 20,000.00 ለሎት ሁለት 50,000 የጨረታ ማስከበርያ በCPO, በሁኔታ ላይያልተሰመረተ የባንክ ዋስትና በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና ጥሬ ገንዘብ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያትዕዛዝ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
  7. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁትፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው።
  8. በዶክሜንቱ ከተጠቀሰው ስፕስፍኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም።
  9. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበርያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክዋስትና የውል ማስከበርያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ5 ቀን ውስጥ ውል አስሮበዶክሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል።
  10. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግስትግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንጽፍ
  11. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም።
  12. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው።
  13. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንድ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  14. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት

14.1 ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም።

14.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል።

15. ጽ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ ትግራይ መቐለ

ስልክ ቁጥር 034 440 73 35/ 0914 75 58 45

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo