መቐለ ዩኒቨርስቲ የማማከርና ንግድ ኢንተርፕራይዝ ለእንስሳት ምግብነት የሚውል የነጭ ወይም ቀይ የራያ ወይም የሁመራ ማሽላት ትራፊ (Maiz by product) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

መቐለ ዩንቨርስቲ

 1 የዘመኑ ግብር የከፈሉ

2 የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸዉ

3 የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ እና የኣቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማረጋገጫ የሚያቀርቡ፤

4 የጨረታ ማስከበሪያ ስፒኦ ብር 5000.00 (ኣምስት ሺ ብር) ማስያዝ የሚችሉ፤

5 አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ንብረቱ በ10 ቀን ዉስጥ በራሳቸዉ ትራንስፖርት መቐለ ዩኒቨርሰቲ እንዳየሱስ ግቢ ወደ ሚገኘዉ የኢንተርፕራይዙ ቢሮ ማቅረብ የሚችሉ

6 የተዘጋጀዉን ዝርዝር መግለጫ ወይም ስፐስፊኬሽን ከኢንተርፕራይዙ ቢሮ የኣቅርቦትና ፋሲሊቲ ክፍል 15/04/2011 ዓ/ም ጀምሮ ብር 50.00 በመክፈል መዉሰድ የሚችሉ ሲሆን ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳችሁ ለጨረታ ተብሎ በተዘጋጀዉ ሳጥን በጨረታዉ ቀናት ማስገባት አለባችሁ።

7 ጨረታዉ 15/04/2011 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 03/05/2011 ዓ/ም በኣየር ቆይቶ ከሰዓት ልክ 9:00 ሰዓት ተዘግቶ፤ በተመሳሳይ ቀን 03/05/2011 ዓ/ም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ከቀኑ 9:30 ይከፈታል።

8 ኢንተርፕራይዙ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታዉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።

መቐለ ዩኒቨርሲቲ እንዳየሱስ ካምፓስ ቅርስ ጥበቃና ጥንተ ምሕዳር ህንፃ፤

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0935-406030/0348-409776 ደውለው መጠየቅ ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo