በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ

የጨረታ ማስታወቂያ

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር  የማዕከላዊ  ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የተለያዩ ያገለገሉ  ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥይፈልጋል።

በጨረታው ለመሳተፍ  የምትፈልጉ ድርጅቶች ሆነ ግለሰብ ከዚህ በታች የተገለፁትን መመሪያዎችና ግዴታዎች ማሟላትአለባቸው።

የጨረታው መመሪያ

  1. ዕቃዎቹን ለመግዛት የሚጫረት  ማንኛውም ድርጅት ሆነ ግለሰብ  ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 5,428.00 (አምስት ሺህ አራት መቶ ሀያ ስምንት ብር)በሲፒኦ (በጥሬ ገንዘብማስያዝ አለበት።
  2. ተጫራቾች  የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን ማረጋገጫ  ማቅረብ የሚችሉ መሆንአለባቸው።
  3. ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው እያንዳንዱ ያገለገሉ  ዕቃዎች ዋጋ በማስቀመጠ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ በግልፅ መፃፍ ይኖርባቸዋል።
  4. ዕቃዎቹ በሚገኙበት ቦታ በመገኘት የሚሸጡትን  ዕቃዎች ዝርዝር ሁኔታ መመልከት ይችላሉ።ሽሬ እንደስላሴ ማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ሱር ካምፕ፣ሽሬ እንደስላሴ ማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ጉና ድፖ
  5. ጨረታውን ያሸነፈ ድርጅትም ሆነ ግለሰብ  ዕቃዎቹን  በ15 ቀናት ውስጥ  ሙሉ በሙሉ አጠቃሎ ማንሳት አለበት።
  6. ጨረታውን ያሸነፈ ድርጅትም ሆነ ግለሰብ  በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ  ዕቃዎቹን አጠቃሎ  ካላነሳ በየቀኑ 300.00ብር ቅጣት ይከፍላል።
  7. የጨረታ ሰነዱን ከተጫራቾች ዝርዝር መመሪያ ጋር የማይመለስ ብር 100.00 ብር በመክፈል ይህ ማስታወቂያበጋዜጣ  ታውጆ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ሰዓት ባሉት ቀናት ውስጥ  ሽሬ በሚገኘው የማዕከላዊ  ዕዝ ጠቅላይ መምሪያንብረት ቡድን ቢሮ መግዛት ይችላል።
  8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ሽሬ ከተማ  በሚገኘው ማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ መዝናኛ ክበብ ውስጥ ለዚሁበተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  9. ጨረታው ታህሳስ 22 ቀን 2011ዓ.ም ከጠዋቱ 400 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 430 ሰዓት ተጫራቾች ወይም  ህጋዊወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  10. አሸናፊ ድርጅቶች ሆነ ግለሰብ ውል ሲፈፅሙ  ያሸነፈበትን ዋጋ ወደ ማዕከላዊ ዕዝ/መምሪያ ፋይናንስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  11. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን  በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀነው።

ለበለጠ መረጃ፡ - በስልክ ቁጥር  034 8 44 07 61/0910354733 ይደውሉ

የማ/ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ሽሬ እንዳስላሴ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo