የመከላኪያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለመቀሌ ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ ፕሮጀክት መቐለ ኣዋሽ ካምፕ ፊት ለፊት ለሚገነባው የመከላከያ ሪፈራል ሆስፒታል የግሪነሪ ሰራዎችን (Greenery Works) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል። በመሆኑም

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ

1 ተጫራቾች በ “Greenery” ስራ ዘርፍ በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የስራ ፍቃድ ያላቸው፤ እና በዘርፉ በቂ የስራ ልምድ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤

2 በተጨማሪም ተጫራቾች የሚያቀርበውን ሳር፣ ዛፍ እና አበባ ከየት እና በምን ኣይነት ኣቀራረብ ሊያስገባ እንደሚችል እንዲሁም የስራውን ሂደት ክንውን የሚገልፅ ዝርዝር የስራ ኣካሄድ በግልፅ ሊያስረዳ የሚችል የስራ ሂደት መግለጫ (Working Methodology) በጥራት እና በተደራጀ ኣቀራረብ ማቅረብ የሚችሉ፤

3 በግሪነሪ ስራ ማለትም ሳር፣ ዛፍ፣ ኣበባ በመትከል ከ30,000  በላይ የሰራ፣ የመልካም ስራ ማስረጃው የሰራበትን ውለታ ኣልያም ከኦርጂናል ጋር የተገናዘበ ከክፍያ ሰነድ ማቅረብ የሚችል፤

4 የጨረታ ማስያዣ 300,000.00 ብር ሲፒኦ ማስያዝ የሚችሉ በተጨማሪም ቫት ተመዝጋቢ የሆናችሁ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤

5 የስራ ዝርዝር መግለጫ ከፕሮጀከቱ ፅ/ቤት በማቅረብ ሰነዱን የማይመለስ 200.00 ብር በመክፈል መግዛት ኣለባቸው።

6 ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን በስም በታሸገ ፖስታ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን 01/04/2011 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 08/04/2011 ዓ/ም እሰከ 8:00 ሰዓት ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።

7 ጨረታው ከ08/04/2011ዓ/ም 8:30 ይከፈታል።

8 ድርጅቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ይሁን በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ ማብራሪያ- የጨረታ ቦታ መቐለ ኣዋሽ ካምፕ ፊት ለፊት ለሚገነባው የመከላከያ ሪፈራል ሆስፒታልፕሮጀክት

ለበለጠ ማብራሪያ /0914-709013 ደውለው መጠየቅ ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo