ድርጅታችን መከላኪያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የመቐለ ባለ ሦስት ኮከብ ሆቴል ፕሮጀክት የworks ስራ ማሰራት ስለሚፈልግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን 01/04/2011 ጀምሮ እስከ 05/04/2011 ዓ/ም ከጧቱ 4:00 ደረስ የምትወዳደሩበት ሰነድ በጨረታ ሳጥን በማስገባት እንድትወዳደሩ እየጋበዝን ጨረታውን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ 05/04/2011 ዓ/ም በጧት 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:30 ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እየገለፅን ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው መመዘኛዎች ከ1-12 ቁጥር የተገለፁ ነጥቦች ይሆናሉ።

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ

ተጫራቶች ማሟላት የሚገባቸው ነጥቦች

1 የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ፤

2 በዘርፉ ህጋዊ የስራ ፍቃድ ያላቸው፤

3 የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፤

4 TIN NO ሰርተፊኬት ኮፒ ማቅረብ የምትችሉ ፣ የቫት ተመዝጋቢ የሆናችሁ

5 የጨረታው ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 (ኣንድ መቶ ብር) መገዛት ኣለባቸው።

6 በ Metal works የስራ ልምድ ማቅረብ ኣለባቸው።

7 ተጫራች ወይም ሀጋዊ ወኪሎቻቸው ከሌሉ የጨረታ ሰነድ የተሟላ ከሆነ ይከፈታል።

8 የጨረታው ማስከበሪያ ሲፒኦ 5000.00 (ኣምስት ሺ ብር) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።

9 በጨረታው ሰነድ ስርዝ ድልዝ ካለ ተወዳዳሪው ከጨረታው ውጭ ይሆናል።

10 የምታስገቡት ዋጋ ከቫት በፊት ወይም ከቫት በኃላ መሆኑ በግልፅ መቀመጥ ኣለበት።

11 የጨረታው ሰነድ በኦርጂናል እና በኮፒ ለየብቻው በማሸግ ማቅረብ ኣለበት።

12 የጨረታው ሰነድ ከፕሮጀክቱ ቢሮ መግዛት ኣለባቸው።

ድርጅቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ኣድራሻ :-ኣክሱም ሆቴል ፊት ለፊት የድሮ ደጀን ሆስፒታል ግቢ ቢሮ ኣሰተዳደር

ስልክ ቁጥር 0344-400242 ወይም 0910-280150

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo