የትግራይ ልማት ማሕበር በመደባይ ዛና ፣ ላዕላይ ማይጨውና ታሕታይ ማይጨው ወረዳዎች የትምህርትና የጤና ተቋማዎችና በስምንት ሉቶች በመከፋፈል ማሰራት ይፈልጋል።

የትግራይ ልምዓት ማሕበር

በዚህ መሰረት

1 ደረጃዎች GC/BC-4 ከዚያ በላይ (ለሎት 01) ፣ GC/BC-5 ከዚያ በላይ (ለሎት 02-08) የሆኑ የ2011ዓ/ም የኮንስትራክሽን ፍቃዳዎችና የንግድ ስራ ፈቃዳቸው ያሳደሱ፣ በኮንስትራክሽን ኣቅራቢነትና ሰርቲፊኬት ያላቸው፣ የቫት  ሰርቲፊኬት፣ የቲን ሰርቲፊኬትና የመጨረሻ ወር የቫት ዲክለሬሽን የሚያቀርቡ ፣ ቴክኒካልን ዶክመንት ጋር ተያይዞ ካልቀረበ ከውድድር ውጭ ይሆናል።

2 የጨረታው ማሰከበሪያ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው የታወቁ ባንኮች 100000.00 (የኣንድ መቶ ሺ ብር) (ሎት01)፣ 50000.00( ኣምሳ ሺ ብር) (ለሎት 02-08) በሲፒኦ ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

3 ተጫራቾች ለሚሰሩት የህንፃ ፕሮጀክት ሳይት ከተረከቡበትን ቀን ጀምሮ በ210 ( ሁለት መቶ ኣስር) ተከታታይ ቀናት ኣጠናቆ ማስረከብ የሚችሉ፤

4 የጨረታው ዶክመንት ከ28/03/2011 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 19/04/2011ዓ/ም ኣስፈላጊውን ዶክመንት በመያዝ የማይመለስ ብር 500.00 (ኣምስት መቶ ብር) በመክፈል ከትግራይ ልማት ማህበር ዋና ፅ/ቤት ቢሮ ቁጥር 435 መውሰድ ይችላሉ።

5 የጨረታው ሰነድ በተጫራቾች መመርያ ተሞልቶ ፣ ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዶክመንቶች ኦርጅናሉና ሁለቱ ፎቶ ኮፒዎች፣ ሲፒኦ ለየብቻቸው በፖስታ ታሽገው በኣንድ ትልቅ ፖስታ ውስጥ ተከተውና በላይ ላዩ ለሚጫረቱት ፕሮጀክት /ሎት ስም በሚታይ ቀለም ፅፈው በሁሉም ዶክመንት (ኣጠቃላይ ላይ ተፈርሞበትና ህጋዊ የሆነ ማህተም በመምታት እስከ 19/04/2011 ዓ/ም ጧት 3:30 ሰዓት በትግራይ ልማት ማህበር ዋናው ፅ/ቤት ለዚሁ ኣገልገሎት የተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

6 ኣንድ ተጫራቾች ከኣንድ ሎት በላይ ዶክመንት መግዛትም ሆነ መወዳደር ኣይችልም፤ ከት.ል.ማ ህንፃ ፕሮጀክት ወስዶ ይህ የጨረታ ሰነድ ኣየር ላይ እስከዋለበት ቀን ድረስ ፊዚካል ኣፈፃፀሙ እንዲሁም ከ 70% በታች የሆነ ፕሮጀክት ያለው ተጫራች ጨረታ ዶክመንት መግዛትም ሆነ መወዳደር ኣይችልም።

7 ጨረታው ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባሉበት 19/04/2011ዓ/ም ከጧቱ 4:00 ሰዓት በተጠቀሰው ቦታ ይከፈታል።

8 ኣሰሪው ፅ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው ኣይገደድም።

ለበለጠ መረጃ ስ.ቁጥር 0344-406840 መጠየቅ ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo