ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም ዓ/ማ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም

ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም ዓ/ማ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በጨረታ  አወዳድሮ  ለመግዛት  ስለ ፈለገ የ2011 ዓ.ም የመንግስት ግብር የከፈሉበትን እና ቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እንድትወዳደሩ እንጋብዛለን፡፡

  1. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ የሚሆን ከጠቅላላ ዋጋ 2% ለድርጅቱ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (CPO) ገቢ ማድረግ ይኖርባችዋል፡፡
  2. የጨረታው ማስከበሪያ ከ2% ያነሰ ያስያዘ ከጨረታው  የሚሰረዝ ይሆናል፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታዉ ዶክሜንት መቐለ በሚገኘዉ የድርጅቱ ዋና መ/ቤት 4ኛ ፎቅ ቢሮ   ቁጥር 409 ወይም አዲስ አበባ በሚገኘዉ ተክለሃይማኖት ቅርንጫፍ ብር 100 በመክፈል  24/03/2011   ዓ.ም ጀምሮ በስራ ሰዓት መዉሰድ እንደምትችሉ እንገልፃለን፡፡
  4. በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተወዳዳሪዎች በታሸገ ኢንቨሎፕ መቐለ ዋና መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን እስከ 3/04/2011 ዓ.ም ከቀኑ 3፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ትችላላቹህ፡፡
  5. በድርጅቱ የቀረበውን ሰነድ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት እንዲሁም የተሟላ ዶክሜንቱ ከሆነ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በይኖሩም 3/04/2011 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡30 ሰዓት    መቐለ በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት ይከፈታል፡፡
  6. የጨረታው አሸናፊ የጨረታው ውጤት እንደተገለፀ ከጠቅላላ ዋጋ 10% performance bond   ማስያዝ    ይኖርበታል፡፡
  7. የጨረታው አሸናፊ የጨረታው ውጤት እንደተገለፀ በ5 ቀን ውስጥ ውል ማሰር ይኖርበታል፡፡
  8. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  9. ለበለጠ መረጃ ዋና ቢሮ ሶስተኛ ፎቅ ቁጥር 11 ወይም በስልክ ቁጥር 0342-40-00-14 መቐለ ዋና ቢሮ ደውለው ማረጋገጥ የምትችሉ መሆናችሁን እንገልፃለን፡፡

ስልክ ቁጥ 251-34 4410250/418281 Fax +251-344 406099

E-mail decsi@ethionet.et               website. www.decsimfi.com.et

    መቐለ- ትግራይ- ኢትጵያ             Mekelle---Tigray----Ethiopia

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo