መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃላ/የተ/የግል/ኩባንያ (MIE) ኤሌክትሮድ ማይልE6013, Ø3.2* 350mm, ፖሊሽንግ ዲስክ180*22mm እና ብርጭቆ ወረቀት(Sandpaper canvas P60 ) በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ብቃት ያላችሁ እና ከዚህ በታች የተዘረዝሩትን መስፈርት የምታሟሉ ተወዳዳሪዎችን እንድትሳተፉ ኩባንያውን በኣክብሮት ይጋብዛል።

መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

የጨረታው መስፈርት

1 ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ  ስራ ፈቃድ ያላቸው :  የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የወሩ ቫት ማሳወቂያ ኦርጂናል እና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ የጨረታው ሰነድ በስራ ሰኣት ከመቐለ ዋና ቢሮ ኢንዳስትሪ ኢክፑመንት ማኑፋክቸሪንግ ቢዝነስ ዩኒት ሳፕላይ መምሪያ ወይም ኣ/ኣበባ ሳሪስ በሚገኘው ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት መውሰድ ይችላሉ።

2 ተጫራቾች የጨረታው ዋጋ በሰም በታሸገ ፖስታ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ከ03/12/2018 እ.አ.አ ጀምሮ እስከ 24/12/2018 እ.ኤ.አ ከሰኣት በኃላ 8:00 ሰዓት ጀምሮ መቐለ ዋና መስሪያ ቤት ወይም ኣዲስ ኣበባ ሳሪስ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ለዚህ ተብሎ በታዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።

3 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (CPO) ለማይልድ ኤሌክትሮድ ብር 40,000.00 (ኣርባ ሺ ብር) ፣ የፖሊሺንግ ዲስክ ብር 6000.00 (ስድስት ሺ ብር)፣ እንዲሁም ለብርጭቆ ወረቀት 6000.00 (ስድስት ሺ ብር) በስም በታሸገ ፖስታ ከጨረታ ጋር ማስገባት አለባቸው :: በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ እንዲሁም ጥሬ ገንዘብ ተቀባይነት የለዉም።

4 ጨረታዉ 24/12/2018 እ.አ.ኣ ከሰኣት በ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በ25/12/2018 እ.ኤ.አ ከሰኣት በኃላ 8:30 ሰዓት ተጫራቶች ወይም ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በመቐለ መስፍን ዋና መ/ቤት በሚገኝ የስብስባ አዳራሽ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸዉ የተሞላ ከሆነ ባይገኙም ጨረታ ሰነዱ ይከፈታል።

5 ተጫራቾቸ የሚያስገቡት ዋጋ ቫት (VAT) ጨምሮ መሆኑና ወይም አለመሆኑን መጠቀስ አለበት ::ይህ ካልሆነ ያስገቡት ዋጋ ቫት (VAT) እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል።

6 ተጫራቾች ፖሊሽንግ ዲስ እና ብርጭቆ ወረቀት የሚያቀርቡት ባዩት የኩባንያችን ማሳያ መሰረት መሆኑ መገንዘብ ኣለባቸው።

7 ኣሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው ከተነገራቸው ቀን ጀምሮ 05 ቀናት ውስጥ ለእያንዳንዱ እቃ የጠቅላላ ቫትን ጨምሮ 10% የውል ማስከበሪያ የባንክ ዋስትና ( Unconditional bank guarantee) ወይም ሲፒኦ በማሰራት ከኩባንያው ጋር ውል መፈራረም ኣለባቸው። ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ ኣማራጭ ይወስዳል።

8 ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ መጓጓዣ፣ የመጫኛና የመውረጃ ያካተተ መሆን ኣለበት። ኣሸናፊው ተጫራቾች ጨረታውን ኣሸንፈው ውል ካሰሩ ቀን ጀምሮ አያንዳንዱ እቃ በ15 ቀናት ውስጥ ማስረከብ ኣለባቸው።ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ ኣማራጭ ይወስዳል።

9 ተጫራቾች የሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት ኣይፈቀድም።

10 ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት እይቻልም::

11 ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃዎች ኣ/አበባ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ወይም መስፍን ዋና መስሪያ ቤት መቐለ ድርስ መጥተው ማስረከብ ኣለባቸው። ክፍያ በሚመለከት ያቀረቡት በድርጅታችን የጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ በኣስር(10) የስራ ቀናት ውስጥ የሚፈፀም ይሆናል።

12 ኩባንያዉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በክፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነዉ:

ለበለጠ መረጃ ስ.ቁጥር መቐለ +251 0344-406803/6225 ፋክስ 00251 344406225

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo