የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት በክልሉ ለሚገኝ ፍርድ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የተለያየ የቢሮ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ከፍተኛ ፍርድ ቤት

የጨረታ ማስታወቂያ 

የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ለ2011 የበጀት ዓመት በክልሉ ለሚገኝ ፍርድ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የተለያየ የቢሮ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ስለዚሀ በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መስፈርቶችን በማሟላት መወዳደር ትችላላችሁ። 

  1. በዘርፉ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑ ማለት የ2011 ዓ.ም ግብር የከፈሉና ያሳደሱ የመንግሥት ግብር ስለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  2. በክልል ፕላንና ፋይናንስ ቢሮ ወይም በፌዴራል መንግሥት ግዢ ኤጀንሲ የአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ መሆናቸው ማረጋገጫ የሚያቀርቡና መለያ ቁጥር ያላቸው።
  3. ተጫራቾች ተጨማሪ እሴት ታክስ ግብር ከፋይ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  4.  ኢምፖርትና ኤክስፖርት የሚያደርጉ ከሆኑ የተሰጣቸው የአስመጪና ላኪ ማረጋገጫ የሚያቀርቡ 
  5.  ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ ብር 50,000.00/ሃምሳ ሺ/ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ የተረጋገጠ  ቼክ ወይም CPO ወይም በሁኔታዎች ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ የሚችሉ፡-
  6. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የያዘ ሰነድ ለሚጫረቱበት ዓይነት የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ይህ  የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ19/3/2011 ዓ.ም  እስከ 18/4/2011 ዓ.ም  ለ30  ተከተታይ  ቀናት ክፍት ሆኖ ሰለሚቆይ በትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከግዢ ክፍል ቁጥር 23 በመምጣት በመውሰድና በ30 ቀናት ውስጥ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፖ.ሣ.ቁ 328 በአድራሻ በመላክ ወይም በግንባር በመቅረብ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሥራ ሰዓት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር ይችላል። 
  7. ጨረታው በ19/4/2011 ዓ.ም  ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት የጨረታው ሳጥን ታሽጎ በዕለቱ 5፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የተሻለ ቢሆንም ባይገኙም  ግን በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በግዢ  ክፍል ይከፈታል። ሆኖም ግን የመክፈቻው ቀን ሕዝባዊ በዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ከላይ በተጠቀሰው ቦታ ይከፈታል። 
  8. የጨረታ አሸናፊዎች ላሸነፉት እቃ ውል የማሰር/የመግባት/ ግዴታ አለባቸው። በገቡት ውል መሠረትም ይፈጽማሉ በገቡት ውል ሳይፈጽሙ ቢቀሩ በእያንዳንዱ ቀን ካስያዙትየጨረታ ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋ 0.1% ቅጣት ገቢ ያደርጋሉ ወይም በሕግ ይጠይቃሉ። 
  9.  ለቢሮ እቃ በቀረበው የጨረታ ሰነድ የእያንዳንዱ ዓይነትና ብዛት የተገለፀው ቁጥር በ20% ሊጨምርም ሊቀንስም ይችላል። 
  10.  ዋጋ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ቀን ጀምሮ ለ60 ቀናት መሆኑን ማወቅ ይኖርባቸዋል። ይህ የቴክኒክና የፋይናንሻል ግምገማዎች ተጠናቅቀው አሸናፊው እስከ መለየትና ማሳወቅ እንዲሁም የቅሬታ ጊዜ ተጠቃልሎ ካሸናፊው ጋር ውል እስኪታሰር የሚወስደው ጊዜ ማለት ነው።
  11. ተጫራቾች በቀረበው ጨረታ ሰነድ አስተያየት ካላቸው ከጨረታ መክፈቻው ሰዓት በፊት ማቅረብ ይችላሉ። በጨረታው መክፈቻ ጊዜ ከሆነ ግን  ተቀባይነት አይኖረውም። 
  12.  መሥሪያ ቤታችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  13.  በስቶክ/መጋዘን/ ቅድሚያ ያለው ይመረጣል። 

 ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልክ ቁጥር 0344-40-24-20/ 0344-41-12-01
 የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo