ድርጅታችን ከቢረ ኢንተርፕራይዝ ኃ.የተ.የግ.ማህበር / ማጋርመንት ቴክስቴይል ፋብሪካ / የድርጀታችን ከዚህ የተዘረዘሩ የተወሰነ የቴክኒክ ችግር ያለባቸው ተሽከርካሪዎች ማለት ዳፍ፣ ሎብልድ ከነ ተሳቢው፣ ብሎ ቦርድ፣ ሚኒባስ ሁለት፣ ቸክ ኣፕ ኣይሱዚ፣ ፎርክሊፍት ( ኣምስት) ፣ ሪኖ ኣውቶ ሞቢል በጨረታ ኣወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

ከቢረ ኢንተርፕራይዝ ኃ/የተ/የግ/ማ

1 ድርጅታችን ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ እና የሃገር ውስጥ የግቢ ግብር የከፈሉ፤

2 የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 (ኣንድ መቶ ብር) በመክፈል ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰኣት መቀሌ (ኲሓ) በሚገኘው ጋርመንትና ቴክስታይል ፋብሪካችን በመገኘት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።

3 ጨረታው ከ19/03/2011 ዓ/ም እሰከ 30/03/2011 ዓ/ም ይካሄዳል።

4 የጨረታው ማስከበሪያ ብር 50000.00( ኣምሳ ሺ ብር) በሲፒኦ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።

5 በጨረታ ኣሸናፊ ከመስሪያ ቤቱ ጋር ውል ከፈረመበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ የውሉን ዋጋ 40% በውል ማስከበሪያነት በባንክ የተመሰከረለት ቼክ /ሲፒኦ/ በከቢረ ኢንተርፕራይዝ የግ ማህበር ስም ኣዘጋጅቶ ማስያዝ ይኖርበታል።

6 ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እሰከ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት መቀሌ ( ኲሐ) በሚገኘው ፋብሪካችን በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

7 ተጫራቾች የሚያቀርቡት ጨረታው ከመከፈቱ ኣንድ ቀን በፊት ባሉት ቀናት ኣስቀድሞ ማቅረብ ኣለባቸው።

8 ጨረታው በኣስረኛው የመጨረሻ የስራ ቀን ከቀኑ 10:30 ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪላቸው በተገኙበት ኣስራ ኣንደኛው የስራ ቀናት 4:00 ሰኣት ላይ ይሆናል።

9 የጨረታው ኣሸናፊ ጨረታው ካኣሸነፈበት ጀምሮ በ10 ተከታታይ ቀናት እቃው ማንሳት ይኖርበታል።

10 መስሪያ ቤቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ በስ.ቁጥር 0344-420830/0344-420550

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo