የኢትዩጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የትግራይ ኣህጉር ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት የቤተክርስትያን ደን ልማት ፕሮጀክት የውሃ ሞተር ፓምፕ ኣወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮምሽን የትግራይ አህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ/ቤት

1 በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው።

2 የ2010 ዓ/ም ግብር  የከፈሉና የዓመት ንግድ ፍቃድ ያሳደሱ::

3 ተጨማሪ እሴት ታክስ  ከፋይ  የሆኑና ያለፈዉ ወር ተ.እ.ታ የከፈሉበት መረጃ ማቅረብ  የሚችሉ::

4 ተጫራቾች የጨረታዉን ሰነድ የማይመለስ 20.00 / ሃያ ብር/ በመግዛት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 / አስር / ቀናት  ዉስጥ የጨረታ ሰነድ መግዛት  ይችላሉ::

5 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 2000 /ሁለት ሺ ብር / የባንክ ዋስትና ወይም CPO በተለየ ፖስታ ኣሽገው ወይም በኣካል ይዘው መቅረብ የሚችሉ::

6 ጨረታው ማሸነፋቸውን ከተገለፀ ጀምሮ በ10 ቀናት ውስጥ ማስረከብ የሚችሉ፤

7 ተሞልቶ የሚቀርበዉ ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለበትና በድርጅታችን በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ብቻ ተሞልቶ መቅረብ ኣለበት፤ ይህንን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውጭ ይሆናል፤

8 የጨረታዉ ሰነድ ዋናዉና ቅጂ ለየብቻዉ በስም በታሸገ ኢንቨሎፕ ለጨረታዉ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ያስፈልጋል::

9 የጨረታዉ ሳጥን በ 24/3/2011 ዓ/ም ጥዋት 8:30 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጥዋቱ 9:00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ወይም መገኘት የማይችሉ ከሆነ ሰነዳቸዉን በማሟለት በፖስታቸዉ ላይ ይከፈትልኝ ብለዉ ከፈረሙና የድርጅቱ ማህተም ካደረጉ በሌሉበት በትግራይ አህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ /ቤት ይክፈታል::

10 ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በክፊል የመሰረዝ መብቱ  የተጠበቀ ነዉ::

አድራሻ 05 ቀበሌ ኮንደሚኒየም አጠገብ የኦርቶዶክስ የህፃናት ማሳደጊያ ድርጅት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo