በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መቐለ ለ2011 በጀት ዓመት ለፈርኒቸር እቃዎች፣ ለኤሌክትሮኒክስ፣ የፅህፈት መሳሪያ ፣ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

መቐለ ዩንቨርስቲ

1 በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱም በዘመኑ የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።

2 የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል ወይም በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዌብሳይት የተመዘገበ።

3 የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ የተመዘገበና የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል።

4 የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል።

5 ለጨረታ ማስከበሪያ/ቢድ ቦንድ/

6ለፈርኒቸር እቃዎች ብር 60,000/ሎት 1/፣ ለኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ብር 50,000/ሎት 2/፣  ለጽህፈት መሳሪያ እቃዎች ብር 50,000/ሎት 3/

7 በባንክ የተመሰከረለት ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ የሚችል።

8 በቀረበው ዝርዝር ስፔስፍኬሽን መሠረት ማቅረብ የሚችል

9 ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ለዚሁ የተዘጋጀ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።

10 ማንኛውም ተጫራች ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መቐለ ዋና ግቢ ቢሮ ቁጥር 219 መውሰድ ይችላሉ።

11 ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 22ኛው ቀን 3፡30 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ጨረታ ተብሎ የተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።

12 ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀንና ወር ጀምሮ በ22ኛው ቀን ጠዋት 3፡30 ተዘግቶ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ ይከፈታል። በ22ኛው ቀን በዓል ከሆነ ደግሞ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ተመሳሳይ ሰዓት ላይ ይከፈታል።

13 በጨረታው አሸንፎ በወቅቱ ውል ለማያስር የጨረታ አሸናፊ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ቢድ ቦንድ አይመለስለትም። ኢንስቲትዩቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 034 441 2801 ወይም 034 441 9039 ደውሎ ማነጋገር የሚቻል መሆኑን በማሳሰብ ጭምር ነው።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo