የሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም የተለያዩ ዕቃዎች ይዞ የመጣ የጣዉላ ሳጥን : አሮጌ ጣዉላ : ኬብሉ ናብረቱ የተፈታ ድራም ፣ ያገለገለ ጠረጴዛ፣ ያገለገለ ወንበር፣ እና የእንጨት ምሰሶ ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ መሸጥ ይፈልጋል።

ኢትዮ ቴሌኮም

ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው ነገሮች

1 ተጫራቾች የዘመኑ ግብር የከፈሉና የታደሰ የ2010 ዓ/ም ንግድ ፈቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

2 ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ በታወቀ በባንከ የተረጋገጠ ቼክ ወይም ስፒኦ ብር 10,000 ማስያዝ አለበት

3 ተጫራቾች ከ ጥቅምት 29 2011ዓ/ም ሎጀስቲክ እና ፋሲሊቲ ክፍል 4 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 በመምጣት የማይመለስ ብር /ሃምሳ ኣምስት/ 50.00 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከገዙ በኃላ ለሽያጭ የተዘጋጁ ዕቃዎችን አዋሽ የእህል መጋዘን አጠገብ በሚገኘዉ መጋዝን ዉስጥ ለጨረታ የተዘጋጀዉ ዕቃዎችን በኣካል ቦታዉ ድረስ በመሄድ በስራ ሰዓት ማየት ይቻላል።

4 ተጫራቾች ዕቃዎቹን የሚገዙበት የኣንዱ ዋጋ ያለ ቫቱ 15% በማስቀመጥ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ አዘጋጅተዉ ሙሉ አድራሻቸዉ በመግለፅ ሎጂስቲክ እና ፋሲሊቲ ክፍል 4 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 ያዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ጥቅምት 29 ቀን 2011  ዓ/ም እስከ ህዳር 12 ቀን 2011 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ከዚህ በኃላ የሚቀርበዉ ማንኛዉም ሰነድ ተቀባይነት የለውም።

5 ጨረታዉ ፍላጎት ያላቸዉ ተጫረቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ሕዳር 12 ቀን 2011 ዓ/ም  ከቀኑ 8:15 በሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም 5ፎቅ የሚገኘዉ የስብሳባ አዳራሽ ይከፈታል።

6 አሸናፊዉ ተጫራቾች ላሸነፈዉ ዋጋ 15% ቫትን ጨምሮ ገቢ ካደረገ በኃላ በአምስት /5/ የስራ ቀናት ዉስጥ ለጨረታ ተለይቶ የተዘጋጁ  አሮጌ ጣዉላ : የጣዉላ ሳጥን :  ኬብሉ ና ብረቱ የተፈታ ድራም ብቻ  በስራ ሰዓት ማንሳት ኣለባቸው። ሆኖም ግን  በጊዜ ገደብ ካላነሱ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ስፒኦ ተደርጎ ሪጅኑ የራሱን አማራጭ ይወስዳል።

7 ዕቃዎቹ በሙሉ ካልሆነ በከፊል መጫረት ኣይችሉም።

8 መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

9 አንድ ተጫራች ባቀረበዉ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም

ስልክ ቁጥር 0344-413134

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo