የትግራይ ክልል ዕቅድና ፋይናንስ ቢሮ ለ2011 የበጀት ዓመት በክልሉ ለሚገኙ ወረዳዎችና ክልል ሴክተሮች ኣገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ሞተር ሳይክል በግልፅ ጨረታ ኣወዳደር ለመግዛት ይፈልጋል። በዚሁ መሰረት በጨረታው መወዳደር የሚፈልግ ማነኛውም ህጋዊ ተጫራች ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች በማሟላት ማቅረብ ይኖርበታል።

የትግራይ ክልልት እቅድና ፋይናንስ ቢሮ

ስለዚህ ከዚህ ቀጥሎ በተጠቀሰው የጨረታ መመሪያ መሰረት በማድረግ የጨረታ ዋጋ በማቅረብ እንድትወዳደሩ እያሳሰብን-

1 በዘርፉ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑ 2010/2011 ዓ/ም ያሳደሱና የመንግስት ግብር ስለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ቫት አና ኣቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ መሆናቸው ማረጋገጫ የሚያቀርቡ በክልል ፐላንና ፋይናንስ ቢሮ ወይም በፌደራል መንግስት ግዢ ኤጀንሲ የኣቅራቢነት ምዝገባ ቲን ቁጥር ያላቸውና ማስረጃ የሚያቀርቡ

2 ተጫራቾች የጨረታው ማስከበሪያው ቢድ ቦንድ ብር 125,000.00 (ኣንድ መቶ ሃያ ኣምስት ሺ ) በባንክ  በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም ሰርቲፋይድ ቼክ በትግራይ ክልል ዕቅድና ፋይናንስ ቢሮ (Bureau of plan & finance) ስም በመዘጋጀት መወዳደር የሚችል-

3 ተጨራቾች የጨረታ ዝርዝር መምሪያ ሰነድ የማይመለስ ብር 150.00 ( ኣንድ መቶ ኣምሳ ብር) በመክፈል ከቢሮ ቁጥር 2.01/2-19 በመውሰድ ዋጋ ማቅረቢያ ሰነዶቻቸውን በስም በታሸጉ ኢንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ከ22/02/2011 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 07/03/2011 ዓ/ም ድረስ በስራ ሰዓት ለክልሉ ዕቅድና ፋይናንስ ቢሮ ፖ.ሳ.ቁ 280/21 በኣድራሻ በመላክ ወም በግንባር በመቅረብ በቢሮ ቁጥር 2.19 ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር ይችላሉ።

4 ጨረታውን በ 15ኛው ቀን በ 07/03/2011 ጥዋት 8:00 ሰዓት ከታሸገ በኃላ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የተሻለ ቢሆን ባይገኙም በ8:30 ሰዓት በክልሉ ፕላንና ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 2.19 ይከፈታል።

5 የጨረታው ማስከበሪያው ቢድ ቦንድን የውል ማስከበሪያው ቢድ ቦንድ ሊሆን ኣይችልም።

6 የሞተር ሳይክል ኣሸናፊዎች ላሸነፉት ስራ ውል የማሰር (የመግባት) ግዴታ ኣለባቸው። በገቡት ውል መሰረትም ይፈፅማሉ። በገቡት ውል ሳይፈፅሙ በቀሩ በእያንዳንዱ ቀን ካስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋ 0.1 & በመቀጣት ገቢ እንዲያደርጉ ይደረጋል ወይም በህግ ይጠየቃሉ።

7 ጨረታው  ከተከፈተ በኃላ በቀረበው የጨረታ ሰነድ መሰረት ሞተር ሳይክሉ ብዛት 20% የተገለፀው ቁጥር ሊጨምርም ሊቀንስም ይችላል።

8 የሞተር ሳይክሉ ግዢ ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ኣሸናፊው ከታወቀው (ከተነገረው) ውል ከታሰረ ቀን ጀምሮ ለ45 ቀናት መሆኑ ማወቅ ይኖርባቸዋል።

9 ተጫራቾች በቀረበው ጨረታ ሰነድ ኣስተያየት ካለዎት ከጨረታ መክፈቻው ሰዓት በፊት ማቅረብ ይችላሉ ካልሆነ በጨረታው መክፈቻ ግዜ ከሆነ ተቀባይነት ኣይኖረውም።

10 ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስ.ቁጥር 0344-415291/0344-407381 ደውለው መጠየቅ ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo