በትግራይ ክልል ዞን ሰ/ምዕራብ ከተማ ሽራሮ ማዘጋጃ ቤት የተለያዩ የልማት ስራዎች ግልጋሎት የሚውል ሎደር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የሽራሮ ከተማ መዘጋጃ ቤት

በትግራይ ክልል ዞን ሰ/ምዕራብ ከተማ ሽራሮ ማዘጋጃ ቤት የተለያዩ የልማት ስራዎች ግልጋሎት የሚውል ሎደር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

በዚህ መሠረት፡-

  1. ተጫራቾች አግባብነት ያለው የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ የቫት የምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የቫት ዲክለር፣ የቲን የምዝገባ፣ የዕቃው አቅራቢነት የምስክር ወረቀት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  2. የጨረታ ማስከበሪያ ዝርዝር በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለፀውን መጠን በሲፒኦ ወይም አንኮንዲሽናል ባንክ ጋራንቲ ማስያዝ የሚችል።
  3. ተጫራቾች ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት ብር 100.00 የማይመለስ በመክፈል ከትግራይ ክልል መንገድ ሥራዎች ኢንተርፕራይዝ መቐለ ግዥና ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት መውሰድ ይችላሉ።
  4. የጨረታው ሰነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት ለዚሁ ለተዘጋጀው ሣጥን ማስገባት ወይም በፖ.ሣ.ቁ. 14 መላክ ይችላሉ።
  5. በጨረታው አሸናፊ የሆነው ተወዳዳሪ የውል ማስከበሪያ 10% በባንክ በተረጋገጠ ሰርቲፋይድ ቼክ (CPO) ወይም Unconditional Bank Guarantee በመያዝ በግንባር ቀርበው ውል መፈፀም የሚችሉ።
  6. ጨረታው ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16 ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ይከፈታል። የመክፈቻ ቀኑ በዓል ከሆነ ወደሚቀጥለው የስራ ቀን ይሸጋገራል።
  7. በጨረታው አከፋፈት ስነ-ስርዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙ ይመረጣል።
  8. ጽ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo