ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት የትምህርት ዘመን የሚውሉ በጨረታ ቁጥር 07/2011 የምግብ ግብአት /ዳቦ/ የስፖርት እቃዎች (ትጥቅ) አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት የትምህርት ዘመን የሚውሉ በጨረታ ቁጥር 07/2011 የምግብ ግብአት /ዳቦ/ የስፖርት እቃዎች (ትጥቅ) አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። በዚህ መሰረት፡-

  1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱንም በዘመኑ የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  2. በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል።
  3. ተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ምዝገባ ሰርተፊኬት።
  4. ተጫራቹ TIN ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል።
  5. ለጨረታ ማስከበሪያ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስም እንደሚከተለው ማስያዝ የሚችል ይሆናል፡፡
    * ሎት 1. የዳቦ አቅርቦት ፦ 150,000.00 ( አንድ መቶ አምሳ ሺ ብር ብቻ)
    * ሎት 2. የስፖርት ዕቃዎች (ትጥቅ) 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር ብቻ)
  6. ተጫራቾች የማቅረብያ /የአቅራቢ ሰርተፊኬት የተመዘገቡ መሆን አለባቸው።
  7. ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል በዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ግዥና ንብረት አስተዳደር ፅ/ቤት ቤት ብሎክ 3 ቁጥር 7 መውሰድ የሚችል ሲሆን ዋጋው መቅረብ ያለበት ደግሞ ከዩኒቨርሲቲው የሚሸጥ ኦርጅናል የመምሪያ ሰነድ ማህተም ያለበት ዶክሜንት ማህተም የተጫራቹ በማድረግ ስርዝ ድልዝ የሌለው ዋጋ ብቻ ነው።
  8. የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚሸጥ ይሆናል።
  9. ጨረታው ሳጥን የሚከፈትበት ቀን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመጨረሻ 16ኛው የስራ ቀን 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በ4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት በግልፅ ይከፈታል።
  10. ዝርዝር ስፔስፊኬሽን በድሀረ ገፅ http://WWW.adu.edu.et ማግኘት ይቻላል፡፡
  11. ዩኒቨርሲቲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo