መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዓይደር ኮምፕሬሄኒሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ2011ዓ.ም በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ የሕንፃ መሳሪያ እቃዎች፣ የኤሌክትሪክ እቃዎች፣ የፅዳት እቃዎች፣ የአይት (ICT) ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

መቐለ ዩንቨርስቲ

ጨረታዉ በጋዜጣ የወጣበት ቀን : 5/2/2011

1 የዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ፣

2 የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል ወይም በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዌብሳይት በአቅራቢነት የተመዘገበ፣

3 የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ የሆነ፣

4 የግብር ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የሚያቀርብ ፣

5 ላለማጭበርበር በድርጅቱ ስም ቃለ መሃላ ማቅረብ የሚችል፣

ተ.ቁ የጨረታ አይነት ሎት የጨረታ ማስከበሪያ ባንክ ጋራንቲ ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ
1 የሕንፃ መሳሪያ እቃዎች ሎት-1 80,000.00 ብር
2 የኤሌክትሪክ እቃዎች ሎት-2 80,000.00 ብር
3 የፅዳት እቃዎች ሎት-3 60,000.00 ብር
4 የአይት (ICT) ዕቃዎች ሎት-4 50,000.00 ብር

6. ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላል።

7. ማንኛውም ተጫራች ለዚሁ ተብሎ የተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዓይደር ግቢ በግ/ን/ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 10 በመቅረብ መውሰድ ይችላል።

8. ጨረታው አየር ላይ የሚቆየው ጊዜ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን ጠዋት 3.30 ሰዓት ተዘግቶ 4.00 ሰዓት ላይ ተጫራቶች ራሳቸው ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልፅ ይከፈታል። በ15ኛው ቀን በዓል ከሆነ ደግሞ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።

9. ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

10. ላለማጭበርበር በኮሌጁ ስም ቃለ መሃላ ማቅረብ የሚችል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo