የትግራይ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ሕጋዊ ነጋዴዎች እንድትጫረቱ ይጋብዛል።

ትግራይ ኢንተርፕራይዝ ዉሃ ስራዎች
ሎት ቁጥር ዝርዝር መግለጫ የማስረከቢያ ቦታ
4 የተለያዩ የGI, DCI, fittings, valves… ፓይፖችና መገጣጠሚያዎች የት.ው.ስ.ኮ.ኢ መቐለ መጋዘን
5 የተለያዩ HDPE and Fittings የት.ው.ስ.ኮ.ኢ መቐለ መጋዘን
6 የተለያዩ UPVC ኬዚንጎች የት.ው.ስ.ኮ.ኢ መቐለ መጋዘን
7 የተለያዩ የአሸዋ፣ ልዩ አሸዋ (Special sand) እና ጠጠር (Gravel) ሸረ ፕሮጀክት ቦታ
8 የተለያዩ የአሸዋ፣ ልዩ አሸዋ (Special sand) እና ጠጠር (Gravel) ሽራሮ ፕሮጀክት ቦታ

የዘመኑን የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ የወሩን ቫት ሪፖርት የሚያቀርቡ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) እና የአቅራቢ ሰርተፍኬት ያላቸው።

ጨረታው ከመከፈቱ በፊት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ ወይም ባንክ ጋራንቲ በታሸገ ፖስታ ለብቻው መቅረብ አለበት።

የዋስትና መጠኑ ለሎት 4 ብር 100,000.0 :ለሎት 5 ብር 100,000.00 : ለሎት6 ብር 50,000.00 : ለሎት 7 ብር 100,000.00 እንዲሁም ሎት 8 ብር 100,000.00 በሲፒኦ ወይም በባንክ ጋራንቲ መልክ ማስያዝ አለባቸው።

በጨረታው አሸናፊ የሆነ 10% የጠቅላላ ያሸነፈው ዋጋ ለውል ማስከበሪያነት ማስያዝ የሚችል መሆን አለበት።

ተጫራቾች መቐለ ከተማ ቀበሌ 07 መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጅነሪንግ አጠገብ ከሚገኘው ጽ/ቤታችን በመቅረብብር 200ለእያንዳንዱ ሎት በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከግዢ ክፍል ቢሮ ቁጥር R-01 መውሰድ ይቻላል።

ውድድሩ የሚካሄደው በሎት (Lot) መሆኑን እንገልፃለን።

ተጫራቾች ለሎት 4፣ 5፣ 6፣ 7 እና 8 የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ፋይናንሻልና ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጅናል እና ኮፒ ተብሎ ለየብቻው ተለያይቶ በሰም በታሸገ ፖስታ መቅረብ አለበት።

የጨረታ ሣጥኑ የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ20 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆንበ21ኛው ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓትተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሆኖ ጨረታውን እንዲከፈት የሚያስፈልግ ቅድመ ሁኔታ ከተሟላ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም የጨረታ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት አይስተጓጎልም።

መክፈቻው ቀን እሁድ ወይም ህዝባዊ በዓል ሆኖ ከተገኘ ቀጥሎ በሚመጣው ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ይከፈታል።

ተጫራቾች ማቅረብ ብቻ (Supply only) ለሆኑት ንብረቱን/እንዲሁም የማቅረብና ተከላ (Supply & installation) ለሆኑት ስራውን ሰርተው የሚያስረክቡበት ጊዜ (Delivery Period) በግልፅ በጨረታው ሰነድ ላይ ማስቀመጥ አለባቸው።

ለሎት 4, 5 እና 6 ንብረት ማስረከቢያ ቦታ በትግራይ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን መቐለ መጋዘን (Store) ይሆናል። ለሎት 7 ንብረት ማስረከቢያ ቦታ ሽረ እንዲሁም ለሎት 8 ንብረት ማስረከቢያ ቦታ ሽራሮ ሆኖ ለሎት 7 እና 8 ዋጋ ሲቀመጥ ከነ ትራንስፖርትና ያለ ትራንስፖርት ተብሎ ዋጋ መሙላት አለባቸው።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo