የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መቀሌ ቅ/ጽ/ቤት የሰራተኞች መኪና ሰርቪስ አገልግሎት፣ ሁለት የመኪና ጥገናና ሰርቪስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ የሚከተለውን አገልግሎት ግዥ መፈጸም ይፈልጋል

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን

◔ ሎት አንድ፡- የሰራተኞች መኪና ሰርቪስ አገልግሎት
◔ ሎት ሁለት፡- ሁለት የመኪና ጥገናና ሰርቪስ

1 በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

2 ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ።

3 የዕቃ ወይም አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ።

4 ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለሥልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ።

5 የጨረታ ማስከበሪያብር10,000.00 (አስር ሺህ ብር) በባንክ በተመሠከረለት ቼክ (C.P.O) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ።

6 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ አጠገብ የሚገኘው የትግራይ አካል ጉዳተኞች ማህበር ህንፃ ከሚገኘው የቅ/ጽ/ቤቱ የግዥ፣ ፋይናንስና ቡድን ግራውንድ ላይ ቢሮ ቁጥር 37 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።

7 ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግጥቅምት 5 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታውም በዚሁ እለትከጠዋቱ 4፡30 ሰዓትበመስሪያ ቤቱ አዳራሽ ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

8 የጨረታው አሸናፊ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ) C.P.O በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል።

9 መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

10 የመኪና ጥገና እና ሰርቪስ ተወዳዳሪዎች በተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባችኋል።

11 የመኪና ጥገና እና ሰርቪስ ተወዳዳሪዎች ደረጃ 4 እና ከዛ በላይ መሆን ይጠበቅባችኋል።

12 የመኪና ጥገናና ሰርቪስ ተወዳዳሪዎች መቐለ ከተማ ውስጥ መሆን ይጠበቅባችኋል።

ለበለጠመረጃ፡- ስልክቁጥር 034 441005/0919 06 83 85

ፋክስቁጥር 034 440 73 09

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo