ድርጅታችን ትግራይ ዉሃ ስራዎች ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ የተለየያዩ ላይሰንሰድ ሶፍት ዌር እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ስለዚህም ከዚህ በታች ያሉ መስፈርቶችና ግዴታዎች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች የማይመለስ 20.00 ብር በመክፈል ድርጅታችን ያዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ወስዳቹህ እንድትወዳደሩ ጥሪ እናቀርባለን።።

ትግራይ የውሃ ስራዎች ጥናት, ዲዛይንና ቁጥጥር ድርጅት

1 ተጫራቾች በዘረፉ የ2010 ዓ/ም ግብር የከፈሉበት የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ የኣቅራቢነት ምስክር ወረቀት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፊኬት የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆኑን የሚረጋግጥ የመስክር ወረቀት ኮፒ ማቅረብ የሚችል

2 የሚቀርበው የጨረታ ሰነድ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማሸግ ለያንዳንዱ ተፈርሞበት በፖስታው ላይ አቅራቢ ድርጅት ሙሉ ስም ፣ኣድራሻ፣ህጋዊ ማህተም፣የጨረታው ዓይነትና የኣጫራች መ/ቤት ስም በመግለፅ ይህ ማስታወቂየ ከወጣበት ቀን ከ25/01/2011ዓ/ም -09/02/2011ዓ/ም ድርጅቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።

3 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከታወቀ ባንክ ብስፒኦ 3000 ብር ጨረታዉ በመኪፈትበት ግዜ ማቅረብ አለባቸዉ

4 ጨረታዉ የሚቆይበት ግዜ 25/01/2011 ዓ/ም እስከ 09/02/2011 ዓ/ም ሲሆን የጨረታ ሳጥን የሚዘጋበት 09/02/2011 ከቀኑ 8:30 ሰዓት ተዘገቶ በዚሁ ቀን 9:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይከፈታል ሆኖም ተጫራቾች በራሳቸዉ ምርጫ በመኪፈትበት ግዜ ሳይገኙ በመቅረታቸዉ የጨረታዉ መከፈት አይስተጋጎልም

5 ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በኣል ከሆነ በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ በቀጣይ ቀን ይከፈታል።

6 ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት ጨምሮ መሆኑና ኣለመሆኑ በግልፅ መጥቀስ ኣለበት።ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተደረጎ ይወስዳል።

7 ድርጅት ካቀረበዉ ስፐስፊኬሽን ዉጭ ያቀረበ ተጫራች ተቀባይነት የለዉም

8 ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን ኣሳልፎ መስጠት ኣይቻልም።

9 ተጫራቾች ኣሸናፊ መሆናቸው ከታወቀ በኃላ ውል ካሰሩ በ30 ቀናት ውስጥ ማቅረብ የሚችሉ።

10 ድርጅቱ የተሻላ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

ለተጨማሪ ማብራሪያ ኣድራችን ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ ኣጠገብ የትግራይ ጦር ጉዳተኞች ማህበር 4 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 9 ስልክ ቁጥር 0344 418556 መጠየቅ ይቻላል

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo