የኢትዮጵያ መንገድ ፈንድ በትግራይ ክልል ለሚገኙ የገጠርና ከተማ የመንገድ ኤጀንሲዎች ለመንገድ ጥገና የ2011 ዓ.ም በጀት የመደብ ሲሆን ከዚሁ ከተመደበው በጀት ውስጥም ለመንገድ ኤጀንሲዎች ለሚሠሩት የመንገድ ጥገና ሥራ የኮንስልታንሲ ሰርቪስ ጨረታ አጫርቶ ለመንገድ ኤጀንሲዎች እንዲያቀርቡ የትግራይ ክልል ኮንስትራክሽንና መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ለዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መንገድ ልማትና አስተዳደር ከኢትዮጵያ መንገድ ፈንድ በተሰጠው ሙሉ ውክልና መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘረውን ማሟላት የሚችሉ ሁሉ በጨረታ መሳተፍ ይችላሉ።

የትግራይ ክልል ኮንስራክሽን መንገድ ትራንሰፖርት ቢሮ

1 የ2010 ዓ.ም የታደሰ የአማካሪነት ንግድ ሥራ ፍቃድ፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የባለፈው ወር ዲክላሬሽን፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) የ2010 ዓ.ም የአቅራቢዎች ምስክር ወረቀት ፍቃድ ያላቸው ሕጋዊ አማካሪዎች በተጨማሪ ከኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የ2010 ዓ.ም የታደሰ የአማካሪ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል።

2 በመንገድ ፈንድ ሙሉ ውክልና የተሰጠው የትግራይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መንገድ ልማትና አስተዳደር በHighway and bridge consultancy and office for consulting engineer General ደረጃ- 3 እና ከዚህ በላይ አማካሪዎች።

3ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፈቀደላቸው ከታወቁ ባንክ በሚሰጥ የተረጋገጠ Unconditional bank guarantee ሲፒኦ ወይም በካሽ ብር20,000 ብር (ሃያ ሺህ)ማቅረብ ይገባቸዋል።

4 ተጫራቾች ለተጫረቱበት Consultancy Service for the Supervision and contract Administration of Road Maintenance Program for Tigray region Urban and rural Agencies የሥራ ውል ከተፈጸመበት ቀን ጀምሮ በትንሹ ለአሥራ ሁለት ተከታታይ ወራት (12 ወር) ሙሉ በሙሉ ሥራውን ተከታትሎ መሥራት አለበት።

5 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከ24/1/2011 ዓ.ም ጀምሮ ከትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ከመንገድ ልማትና አስተዳደር ከቢሮ ቁጥር 210 አስፈላጊውን ማስረጃ በማስያዝየማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር)በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።

6 ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የፕሮጀክት ዋጋ (ፋይናንሻል) እና ቴክኒካል ዶክመንት አንድ ኦርጅናልና ሁለት ፎቶ ኮፒ በተለያዩ ፖስታዎች ታሽጎ እንዲሁም የ2010 ዓ.ም የታደሰ የአማካሪነት ንግድ ሥራ ፈቃድ ተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀት የባለፈው ወር ዲክላሬሽን፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) የአቅራቢዎች ምስክር ወረቀት ፈቃድ፣ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሁሉንም ጠቅልሎ በሚይዝ ትልቅ ፖስታ በማሸግ እና የተጫረቱበት ፕሮጀክት ስም በትልቁ ፖስታ ላይ በመጻፍ በዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መንገድ ልማትና አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 152 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምር ባሉት 30 ተከታታይ ቀናት /31ኛውን ጨምሮ/ እስከ 24/2/2011 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርበታል።

7 ጨረታው የሚዘጋበት ቀን 24/2/2011 ዓ.ም በ 4፡00 ሰዓት ከሰዓት በፊት ሆኖ በተመሳሳይ ቀን በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 152 በጨረታው ኮሚቴው ይከፈታል።

8 ከተጠቀሰው ሰዓት ዘግይቶ የመጣ ተጫራች ጨረታው ላይ አይሳተፍም።

9 ተጫራቾች ወደ ዋጋ መወዳደሪያ ሰነድ ለመግባት ዝቅተኛው የቴክኒካል ነጥብ ማግኘት አለባቸው። ዝቅተኛ ነጥብ 70% (ሰባ) ሆኖ ዝቅተኛ ነጥብ ያላገኙ ተጫራቾች የዋጋ መወዳደሪያ ሰነዳቸው ሳይከፈት ይመለስላቸዋል።

10 ቢሮው የተሻለ አማራጭ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ፡- ለዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መንገድ ልማትና አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 210 ሦስተኛ ፎቅ ወይም፣አድራሻ፡- ስልክ ቁጥር፡- 0344-41-06-45/0344-40-00-50

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo